عن أبي موسى الأشعري رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«إِذَا مَرِضَ الْعَبْدُ أَوْ سَافَرَ كُتِبَ لَهُ مِثْلُ مَا كَانَ يَعْمَلُ مُقِيمًا صَحِيحًا».
[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...
አቢ ሙሳ አል-አሽዓሪይ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ማለታቸው ተላልፏል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡
"አንድ ሰው በታመመ ወይም ጉዞ በወጣ ወቅት ሀገሩ እያለና ጤናማ ሳለ እንደሚያደርገው አጅር ይፃፍለታል።"
Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]
ነቢዩ ﷺ ስለአሏህ እዝነትና ችሮታ እየነገሩን ነው። ይህም አንድ ሙስሊም በሀገሩ እና ጤነኛ ሳለ እንደልምድ የሚያደርገውን መልካም ስራ ከዚያም ዑዝር ገጥሞት ታሞ ማድረግ ባይችል፣ ወይም በጉዞ ወይም ደግሞ በሌላ በየትኛውም ትክክለኛ ምክንያት ሳያደርገው ቢቀር ልክ ጤነኛና በሀገሩ ሆኖ ሲያደርግ እንደነበረው ምንዳ ሙሉ ሆኖ ይፃፍለታል።