عن جرير بن عبد الله رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«مَنْ لَا يَرْحَمِ النَّاسَ لَا يَرْحَمْهُ اللهُ عَزَّ وَجَلَّ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከጀሪር ቢን ዐብደላህ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አለ: የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ:
"ለሰዎች የማይራራን አሸናፊና የበላይ የሆነው አላህ አይራራለትም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለሰዎች የማይራራ ሰውን የላቀውና የተከበረው አላህም እንደማይራራለት ገለፁ። ሰው ለፍጡር ማዘኑ የአላህን ርህራሄ ማግኛ ከሆኑ ትላልቅ ሰበቦች መካከል ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ርህራሄ ለሌሎቹም ፍጡራን ያስፈልጋል። ነገር ግን ሀዲሱ ላይ ሰውን ብቻ የጠቀሰው አፅንኦት ለመስጠት ነው።
  2. አላህ ለአዛኝ ባሮቹ የሚራራ አዛኝ ጌታ ነው። ምንዳ በስራ አይነት ነው።
  3. ለሰው ማዘን ሲባል ለነሱ መልካም ማድረግን፣ ጉዳትን ከነርሱ ላይ መከላከልንና ባማረ መልኩ ከነርሱ ጋር መኗኗርን ይጠቀልላል።