عَن أَبِي أُمَامَةَ رضي الله عنه قَالَ: سَمِعْتَ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَخْطُبُ فِي حَجَّةِ الوَدَاعِ فَقَالَ:
«اتَّقُوا اللَّهَ رَبَّكُمْ، وَصَلُّوا خَمْسَكُمْ، وَصُومُوا شَهْرَكُمْ، وَأَدُّوا زَكَاةَ أَمْوَالِكُمْ، وَأَطِيعُوا ذَا أَمْرِكُمْ تَدْخُلُوا جَنَّةَ رَبِّكُمْ».

[صحيح] - [رواه الترمذي وأحمد]
المزيــد ...

ከአቡ ኡማማ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህን መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመሰናበቻ ሐጅ ወቅት እንዲህ ብለው ኹጥባ ሲያደርጉ ሰምቻቸዋለሁ፦
"ጌታችሁን አላህ ፍሩ፣ አምስት (አውቃት) ሶላታችሁን ስገዱ ፣ የፆም ወራችሁን ፁሙ፣ የገንዘባችሁንም ዘካ ስጡ፣ መሪያችሁን ታዘዙ፤ የጌታችሁን ጀነት ትገባላችሁ።"

Sahih/Authentic. - [Ibn Hibbaan]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሂጅራ አስረኛው ዓመት በመሰናበቻው ሐጅ ወቅት የዐረፋ ቀን ኹጥባ አደረጉ። በዚህ ስያሜ የተሰየመችው እርሳቸው (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በዚህ ወቅት ሰዎችን ስለተሰናበቱ ነው። ሰዎች ባጠቃላይ ትእዛዛቱን በመፈፀም ክልከላዎቹን በመራቅ ጌታቸውን እንዲፈሩ አዘዙ። በቀንና ምሽት አላህ ግዴታ ያደረገውን አምስት ሶላቶች እንዲሰግዱም አዘዙ። የረመዷንን ወርም እንዲፆሙ አዘዙ። የገንዘባቸውን ዘካ ለሚገባው ሰው እንዲሰጡና በርሱም እንዳይሰስቱ አዘዙ። በነርሱ ላይ አላህ መሪዎች ያደረጋቸውን አካላት አላህን በማመፅ እስካላዘዙ ድረስ ታዛዥ እንዲሆኑ አዘዟቸው። እነዚህን የተጠቀሱትን ጉዳዮች የፈፀመ ሰው ምንዳው ጀነት መግባት እንደሆነ ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. እነዚህ ተግባራት ጀነት ከመግቢያ ሰበቦች መካከል ናቸው።