عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ:
«لَا يَقْبَلُ اللهُ صَلَاةَ أَحَدِكُمْ إِذَا أَحْدَثَ حَتَّى يَتَوَضَّأَ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"አንዳችሁ ዉዱእ በሌለው ጊዜ ዉዱእ እስኪያደርግ ድረስ አላህ ሶላቱን አይቀበለውም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለሶላት ትክክለኝነት ከሚያስፈልጉ መስፈርቶች መካከል ጠሀራ አንዱ መሆኑን ገለፁ። ስለሆነም ሶላት መስገድ በፈለገ ሰው ላይ እንደሰገራ ወይም ሽንት ወይም እንቅልፍና መሰል ሌላ ዉዱእ ከሚያፈርሱ ነገሮች መካከል አንድም አፍራሽ ነገር ከተከሰተ ዉዱእ ማድረግ ግዴታው ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዉዱእ የሌለው ሰው ከትልቁ ሐደሥ በትጥበት፤ ከትንሹ ሐደሥ ደግሞ በዉዱእ እስኪፀዳ ድረስ ሶላቱ ተቀባይነት አይኖረውም።
  2. ዉዱእ ማለት ውሀን አፍ ውስጥ በመያዝ አመላልሶ በመትፋት ከዚያም ውሀን ወደ አፍንጫ ውስጥ መሳብ ከዚያም ማውጣት፤ ቀጥሎ ፊቱን ሶስት ጊዜ ማጠብ፤ ቀጥሎ ሁለት እጆችን ክርንን ጨምሮ ሶስት ጊዜ ማጠብ፤ ቀጥሎ ጭንቅላትን ባጠቃላይ አንድ ጊዜ ማበስ፤ ቀጥሎ ሁለት እግሮችን ከቁርጭምጭሚቱ ጋር ሶስት ጊዜ ማጠብ ነው።