عن معاوية رضي الله عنه قال: سمعت النبي صلى الله عليه وسلم يقول:
«مَنْ يُرِدِ اللهُ بِهِ خَيْرًا يُفَقِّهْهُ فِي الدِّينِ، وَإِنَّمَا أَنَا قَاسِمٌ، وَاللهُ يُعْطِي، وَلَنْ تَزَالَ هَذِهِ الْأُمَّةُ قَائِمَةً عَلَى أَمْرِ اللهِ، لَا يَضُرُّهُمْ مَنْ خَالَفَهُمْ، حَتَّى يَأْتِيَ أَمْرُ اللهِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከሙዓዊያህ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻዋለሁ፦
"አላህ ለእርሱ መልካምን የሻለትን ሰው ሃይማኖቱን ያስገነዝበዋል። እኔ አከፋፋይ ብቻ ነኝ አላህ ነው የሚሰጠው። ይህች ኡማህ በአላህ ትእዛዝ ላይ የቆመች ከመሆን አትወገድም! የአላህ ትእዛዝ እስክትመጣ ድረስም የተቃረናቸው ሁሉ አይጎዳቸውም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

አላህ ለእርሱ መልካምን የሻለት ሰው ሃይማኖቱን መገንዘብ እንደሚቸረው፤ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አላህ ከሰጣቸው ሲሳይ፣ ዕውቀትና ሌሎችም ነገሮች የሚያከፋፍሉና የሚያሰራጩ አከፋፋይ ብቻ እንጂ ትክክለኛው ሰጪ አላህ ብቻ ነው። ከሱ ውጪ ያሉት ከሰበብነት የዘለለ ከርሱ ፈቃድ ውጪ እንደማይጠቅሙ፤ ይህ ኡማህ በአላህ ትእዛዝ ላይ ከመቆም እንደማይወገድና ትንሳኤ እስከሚቆም ድረስም የተፃረራቸው እንደማይጎዳቸው ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሸሪዐዊ ዕውቀት እና እርሱን መማር ያለው ትሩፋት ትልቅ መሆኑንና በርሱም ላይ መነሳሳቱን ተረድተናል፤
  2. በእዚህ ኡማህ ውስጥ በእውነት ላይ የሚቆም መኖሩ የማይቀር ጉዳይ መሆኑን፤ ከእውነተኛ መንገድ አንዱ ሲገለል ሌላው በእውነት ላይ ይቆማል።
  3. ሃይማኖትን መገንዘብ አላህ ለባሪያው መልካም ከመሻቱ የሚመደብ መሆኑን ፤
  4. ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የሚሰጡት በአላህ ትእዛዝና ፍላጎት ብቻ መሆኑንና ያለርሱ ፈቃድ አንድም ነገር ማድረግ እንደማይችሉ ተረድተናል።