عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَا تَصْحَبُ الْمَلَائِكَةُ رُفْقَةً فِيهَا كَلْبٌ وَلَا جَرَسٌ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2113]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"መላእክት ውሻ እና ቃጭል ካላቸው መንገደኞች ጋር አብረው (አይጎዳኙም) አይሄዱም።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2113]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በጉዞ ወቅት በመካከላቸው ውሻ ካለ ወይም በእንስሶች ላይ የሚንጠለጠለውና ሲንቀሳቀስ ድምፅ የሚያወጣው ቃጭል ካለ መላእክት ከነርሱ ጋር በወዳጅነት እንደማይጎዳኙ ተናገሩ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከአደን ውሻና ከጥበቃ ውሻ በቀር ውሻ መያዝና መጎዳኘት መከልከሉን እንረዳለን።
  2. ከመጎዳኘት የሚቆጠቡት መላእክቶች የእዝነት መላእክት ናቸው። የሰውን ስራ የሚቆጣጠሩት መላእክት ግን ባሮችን ቤታቸውም ውስጥ ሆኑ ጉዞ ላይ አይለዩዋቸውም።
  3. ቃጭል መከልከሉን እንረዳለን። ምክንያቱም እርሱ ከሰይጣን መዝሙሮች መካከል አንዱ ነውና። ቃጭል በውስጡ የክርስቲያኖች ደወል ጋር መመሳሰልን ያቀፈ ነው።
  4. አንድ ሙስሊም መላእክትን የሚያርቅ ከሆነ ነገር ሁሉ በመራቅ ላይ ሊጥር እንደሚገባ እንረዳለን።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (54)
ተጨማሪ