+ -

عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«يَقُولُ اللَّهُ تَعَالَى لِأَهْوَنِ أَهْلِ النَّارِ عَذَابًا يَوْمَ القِيَامَةِ: لَوْ أَنَّ لَكَ مَا فِي الأَرْضِ مِنْ شَيْءٍ أَكُنْتَ تَفْتَدِي بِهِ؟ فَيَقُولُ: نَعَمْ، فَيَقُولُ: أَرَدْتُ مِنْكَ أَهْوَنَ مِنْ هَذَا، وَأَنْتَ فِي صُلْبِ آدَمَ: أَلّاَ تُشْرِكَ بِي شَيْئًا، فَأَبَيْتَ إِلَّا أَنْ تُشْرِكَ بِي».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 6557]
المزيــد ...

ከአነስ ቢን ማሊክ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
«የትንሳኤ ቀን ከእሳት ነዋሪዎች እጅግ ዝቅተኛ ቅጣት ለሚቀጣው አላህ እንዲህ ይለዋል: "ምድር ውስጥ የሚገኙ ነገሮች ሁሉ ቢኖርህ ያንን ነገር ፍዳ ታደርገዋለህን?" እርሱም: "አዎን" ይላል። አላህም "በአደም ጀርባ እያለህ ካንተ ከዚህም ያነሰ ነገር ነበር የፈለግኩት: በኔ አንዳችንም አታጋራ ነበር ያልኩህ። አንተ ግን በኔ ማጋራትን እንጂ ሌላውን ነገር እምቢ አልክ።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 6557]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከእሳት ነዋሪዎች መካከል እሳት ከገባ በኋላ ዝቅተኛውን ቅጣት ለሚቀጣው አላህ እንዲህ እንደሚለው ተናገሩ: ላንተ ዱንያና በውስጧ ያሉ ነገሮች ሁሉ ቢኖሩህ ከዚህ ቅጣት ፋንታ እነርሱን ፍዳ አታደርጋቸውምን? እርሱም: አዎን ይላል። አላህም እንዲህ ይለዋል: በአደም ጀርባ ሳለህ እኔ ካንተ ጋር ቃልኪዳን ስወስድ የፈለግኩትና ያዘዝኩህ ከዚህም የቀለለውን ነገር ነበር። እርሱም በኔ አንዳችንም አታጋራ የሚል ነበር። አንተ ግን ወደ ዱንያ ያመጣሁህ ጊዜ ማጋራትን እንጂ እምቢ አልክ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የተውሒድ ትሩፋትንና በርሱ መስራት ቀላልነቱን እንረዳለን።
  2. በአላህ የማጋራት አደገኝነትንና ፍፃሜውን እንረዳለን።
  3. አላህ የአደም ልጆች በአባታቸው አደም ጀርባ ላይ ሳሉ እንዳያጋሩ ቃል ኪዳን ከነርሱ መውሰዱን እንረዳለን።
  4. ከሺርክ መጠንቀቅ እንደሚገባና ከሀዲ ለሆነ ሰው የትንሳኤ ቀን ዱንያ ባጠቃላይ ተሰብስባ አንዳችም እንደማትጠቅመው እንረዳለን።