+ -

عَنْ عَبْدِ اللهِ بْنِ مَسْعُودٍ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لَيْسَ الْمُؤْمِنُ بِالطَّعَّانِ وَلاَ اللَّعَّانِ وَلاَ الفَاحِشِ وَلاَ البَذِيءِ».

[صحيح] - [رواه الترمذي] - [سنن الترمذي: 1977]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"ሙእሚን የሆነ ሰው እጅግ ተቺ፣ እጅግ ተራጋሚ፣ ፀያፍ ተግባር ሰሪ፣ መጥፎ ንግግር ተናጋሪ አይደለም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - - [ሱነን ቲርሚዚ - 1977]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምሉዕ ኢማን ያለው አማኝ ሰዎችን በዘራቸው የሚተች፣ ስድብና እርግማን የሚያበዛ፣ ሃፍረተ ቢስነትን የተላበሰ ፀያፍ ድርጊትና ንግግርን የሚያበዛ እንዳልሆነ ተናገሩ።

ትርጉም: ኢንዶኔዥያኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ታጋሎግ ሃውሳ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በሸሪዓዊ ጥቅሶች ውስጥ ክልክል በመተግበር ወይም ግዴታን በመተው ካልሆነ በቀር ኢማን ውድቅ አይደረግም።
  2. አካላትን በመጠበቅና ከመጥፎ ተግባራት በመታቀብ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። በተለይ ምላስን።
  3. ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: (እጅግ ተቺና እጅግ ተራጋሚ) በማለት ሁለቱ በተጋኖ ቃል መጠቀሳቸው ትችትና እርግማን የሚገባውን ሰው በትንሹ መተቸትና መርገም የኢማን ሰዎችን በኢማን ከመገለፅ እንደማያጎድልባቸው ያስረዳል።