عن عُثْمَانَ بْنَ أَبِي الْعَاصِ رضي الله عنه:
أنه أَتَى النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقَالَ: يَا رَسُولَ اللهِ، إِنَّ الشَّيْطَانَ قَدْ حَالَ بَيْنِي وَبَيْنَ صَلَاتِي وَقِرَاءَتِي يَلْبِسُهَا عَلَيَّ، فَقَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «ذَاكَ شَيْطَانٌ يُقَالُ لَهُ خِنْزَِبٌ، فَإِذَا أَحْسَسْتَهُ فَتَعَوَّذْ بِاللهِ مِنْهُ، وَاتْفُلْ عَلَى يَسَارِكَ ثَلَاثًا»، قَالَ: فَفَعَلْتُ ذَلِكَ فَأَذْهَبَهُ اللهُ عَنِّي.

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከዑሥማን ቢን አቢል ዓስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው
እርሱ ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ በመምጣት "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሰይጣን በኔና በሶላቴ እንዲሁም በቂረአቴ መካከል አዘናጋኝና በኔ ላይ ያለባብስብኛል።" አላቸው። የአላህ መልዕክተኛም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) "ይሄ ሰይጣን ነው። ኺንዘብ ይባላል። ይህ ስሜት የተሰማህ ጊዜ ከርሱ በአላህ ተጠበቅ! ወደ ግራህም ሶስት ጊዜ ትፋ!" አሉት። እርሱም "ይህንን ፈፀምኩ አላህም አስወገደልኝ።" አለ።

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ዑሥማን ቢን አቢልዓስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመምጣት እንዲህ አለ: "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሰይጣን በኔና በሶላቴ መካከል ጋሬጣ ሆነ በርሷ ውስጥ ከመመሰጥም ከለከለኝ። በኔ ላይ ሶላቴ ውስጥ የምቀራውን ቂረአቴን ቀላቀለብኝም አጠራጠረኝም።" የአላህ መልዕክተኛም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉት: "ይህ ሰይጣን ነው። ኺንዘብ ይባላል። ይህንን ያገኘህና የተሰማህ ጊዜ ከርሱ በአላህ ተጠበቅ። ወደ ግራህም ዞረህ ከትንሽ ምራቅ ጋር ሶስት ጊዜ ትፋ።" ዑሥማንም እንዲህ አለ "ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ያዘዙኝን ነገር ፈፀምኩ። አላህም ከኔ ላይ አስወገደልኝ።"

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሶላት ውስጥ መመሰጥና ልብን መጣድ አንገብጋቢ መሆኑን እንረዳለን። ሰይጣንም ሶላት ውስጥ በመወስወስና በመጎትጎት ይታገላል።
  2. ሰይጣን ሶላት ውስጥ በሚወሰውስ ወቅት ወደ ግራ ከመትፋት ጋር ሶስት ጊዜ "አዑዙ ቢላሂ ሚነሽሸይጧኒ አርረጂም" ሶስት ማለት እንደሚወደድ እንረዳለን።
  3. ሶሐቦች (ረዲየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በሚያጋጥማቸው ችግሮች ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ችግራቸውን እስኪፈቱላቸው ድረስ ወደርሳቸው እንደሚመለሱ መገለፁን እንረዳለን።
  4. የሶሐቦች ልብ ህያው መሆኑን እንረዳለን። ሀሳባቸው ሁሉ መጪው አለም ነው።