عن حُذَيْفَةَ رضي الله عنه:
أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ كَانَ يَقُولُ بَيْنَ السَّجْدَتَيْنِ: «رَبِّ اغْفِرْ لِي، رَبِّ اغْفِرْ لِي».

[صحيح] - [رواه أبو داود والنسائي وابن ماجه وأحمد]
المزيــد ...

ከሑዘይፋ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:
"ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለቱ ሱጁዶች መካከል 'ረቢጝፊርሊ ረቢጝፊርሊ' 'ጌታዬ ሆይ! ማረኝ! ጌታዬ ሆይ! ማረኝ!' ይሉ ነበር።"

Sahih/Authentic. - [Abu Dawood]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለቱ ሱጁዶች መካከል በሚቀመጡ ጊዜ "ረቢጝፊርሊ ረቢጝፊርሊ" "ጌታዬ ሆይ! ማረኝ! ጌታዬ ሆይ! ማረኝ!" ይሉ ነበር። ይደጋግሟትም ነበር።
"ረቢጝፊርሊ" ማለት አንድ ባሪያ ከጌታው ወንጀሎቹን እንዲምረውና ነውሮቹን እንዲሸሽግለት መፈለጉ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በግዴታም ሆነ ሱና ሶላት ውስጥ በሁለቱ ሱጁዶች መካከል ይህንን ዱዓ ማድረግ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን።
  2. "ረቢጝፊርሊ" "ጌታዬ ሆይ! ማረኝ" የሚለውን ዚክር መደጋገም እንደሚወደድ እንረዳለን። ግዴታው ግን አንድ ጊዜ ማለት ነው።
ተጨማሪ