عن أَبِي حَازِمِ بْن دِينَارٍ:
أَنَّ رِجَالًا أَتَوْا سَهْلَ بْنَ سَعْدٍ السَّاعِدِيَّ، وَقَدِ امْتَرَوْا فِي الْمِنْبَرِ مِمَّ عُودُهُ، فَسَأَلُوهُ عَنْ ذَلِكَ، فَقَالَ: وَاللهِ إِنِّي لَأَعْرِفُ مِمَّا هُوَ، وَلَقَدْ رَأَيْتُهُ أَوَّلَ يَوْمٍ وُضِعَ، وَأَوَّلَ يَوْمٍ جَلَسَ عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، أَرْسَلَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ إِلَى فُلَانَةَ -امْرَأَةٍ من الأنصار قَدْ سَمَّاهَا سَهْلٌ-: «مُرِي غُلَامَكِ النَّجَّارَ أَنْ يَعْمَلَ لِي أَعْوَادًا أَجْلِسُ عَلَيْهِنَّ إِذَا كَلَّمْتُ النَّاسَ»، فَأَمَرَتْهُ فَعَمِلَهَا مِنْ طَرْفَاءِ الْغَابَةِ، ثُمَّ جَاءَ بِهَا، فَأَرْسَلَتْ إِلَى رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَأَمَرَ بِهَا فَوُضِعَتْ هَاهُنَا، ثُمَّ رَأَيْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ صَلَّى عَلَيْهَا وَكَبَّرَ وَهُوَ عَلَيْهَا، ثُمَّ رَكَعَ وَهُوَ عَلَيْهَا، ثُمَّ نَزَلَ الْقَهْقَرَى، فَسَجَدَ فِي أَصْلِ الْمِنْبَرِ ثُمَّ عَادَ، فَلَمَّا فَرَغَ أَقْبَلَ عَلَى النَّاسِ فَقَالَ: «أَيُّهَا النَّاسُ، إِنَّمَا صَنَعْتُ هَذَا لِتَأْتَمُّوا وَلِتَعَلَّمُوا صَلَاتِي».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሐዚም ቢን ዲናር እንደተዘገበው:
የተወሰኑ ሰዎች የነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሚንበር ከምን አይነት እንጨት ነው የተሰራው? በሚለው ተከራክረው ሰህል ቢን ሰዕድ አስሳዒዲይ ዘንድ መጡ። ስለጉዳዩም ጠየቁት። እርሱም "ወላሂ እኔ ከምን እንደተሰራ አውቃለሁ። መጀመሪያ የተኖረበት ቀንና የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በርሱ ላይ መጀመሪያ የተቀመጡ እለት ተመልክቼዋለሁ። የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ወደ እከሊት (ከአንሷር የሆነች ሴት ስትሆን ሰህል ስሟን ጠርቷት ነበር።) "አናጢውን አገልጋይሽን ለሰዎች ንግግር ሳደርግ የምቀመጥበትን እንጨት እንዲሰራልኝ እዘዢ።" በማለት መልእክት ላኩላት። እርሷም አዘዘችው። እርሱም ሚንበሩን ‹ጦርፋኡል ጛባ› (ጠደቻ) ከሚባለው የእንጨት አይነት ሰርቶ ወደርሷ አመጣ። እርሷም ወደ አላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ላከችው። በርሳቸው ትእዛዝም እዚህ ጋር ተቀመጠ። ከዚያም የአላህን መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እርሱ ላይ ሲሰግዱበት ተመልክቻቸዋለሁ። ሚንበሩ ላይ እንዳሉ ተክቢራ አደረጉ ፣ እዛው ላይ እያሉም ሩኩዕ አደረጉ፣ ከዚያም ወደኋላ ወረዱ፣ ከሚንበሩ ስር ሱጁድ አደረጉና እንደገና ወደ ሚንበሩ ተመለሱ። ሶላቱን ያጠናቀቁ ጊዜ ወደ ሰዎች በመዞር እንዲህ አሉ 'እናንተ ሰዎች ሆይ! ይህንን የፈፀምኩት በኔ እንድትከተሉና አሰጋገዴንም እንድታውቁ ነው።'"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የተወሰኑ ሰዎች ወደ አንድ ሶሐባ የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ንግግር ሲያደርጉ የሚጠቀሙበት ሚንበር ከምን እንደተሰራ ሊጠይቁት መጡ። በዚህ ዙሪያም አየተነታረኩና እየተከራከሩ ነበር። ሱሓቢዩም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አናጢ አገልጋይ ወደነበራት የአንሷር ሴት "ለሰዎች ንግግር በማደርግበት ወቅት የምቀመጥበትን ሚንበር ለኔ እንዲሰራልኝ አገልጋይሽን እዘዢልኝ።" በማለት መልዕክተኛ መላካቸውን፤ እርሷም ትእዛዛቸውን በመቀበል አገልጋዩዋን ለነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከጦርፋእ ዛፍ ሚንበር እንዲሰራ ማዘዟን፤ ያጠናቀቀ ጊዜም ሚንበሩን ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መላኳን እርሳቸውም መስጂድ ውስጥ ቦታው ላይ እንዲቀመጥ አዘው መቀመጡንና ሚንበሩ ላይም መስገዳቸውን አወሳ። ሚንበሩ ላይ ሆነው ተክቢራ አደረጉ፣ እርሱ ላይ እንዳሉም ሩኩዕ አደረጉ፣ ከዚያም ፊታቸውን ወደኋላ አቅጣጫ ሳያዞሩ ወደኋላ እያፈገፈጉ በመውረድ ሚንበሩ ስር ሱጁድ ወረዱ፣ ከዚያም ወደ ሚንበሩ ተመለሱ። በዚህ መልኩ ሰግደው እንዳጠናቀቁም ወደ ሰዎች በመዞር እንዲህ አሉ: "እናንተ ሰዎች ሆይ! ይህንን የፈፀምኩት እንድትከተሉኙና አሰጋገዴን እንድታውቁ ነው።"

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሚንበርን ማዘጋጀትና ኹጥባ አድራጊ እርሱ ላይ መውጣቱ እንደሚወደድ እንረዳለን። ጥቅሙም ድምፅን ማዳረስና ማሰማት ነው።
  2. በማስተማር አላማ ሚንበር ላይ መስገድ እንደሚፈቀድና አስፈላጊ ከሆነ ኢማሙ ከተከታዮቹ ከፍ ማለቱም እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
  3. ለሙስሊሞች ጥቅም ሲባል በሙያተኞች መታገዝ እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
  4. አስፈላጊ ከሆነ ሶላት ውስጥ ትንሽ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
  5. ሶላት ውስጥ ተከታይ የሆነ ሰው ከኢማሙ ለመማር በሚል ወደ ኢማሙ መመልከቱ እንደሚፈቀድና ይህም በተመስጦ ከመስገድ ጋር እንደማይፃረር እንረዳለን።
ተጨማሪ