عن أبي هريرة رضي الله عنه قال:
لَعَنَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ الرَّاشِيَ وَالْمُرْتَشِيَ فِي الْحُكْمِ.

[صحيح] - [رواه الترمذي وأحمد]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
"የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በፍርድ አሰጣጥ ዙሪያ ጉቦ ሰጪንም ተቀባይንም ረገሙ።"

Sahih/Authentic. - [At-Tirmidhi]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጉቦ በሚሰጥ፣ በሚቀበልና በሚበላ ሰው ላይ ከአላህ እዝነት እንዲርቅና እንዲባረር ዱዓ አደረጉበት።
ከዚህም መካከል ጉቦ ሰጪው ያለአግባብ ወደፍላጎቱ ለመዳረስ ሲል ለዳኞች በተሾሙበት ፍርድ እንዲያዘነብሉ (ኢፍትሃዊ እንዲሆኑ) የሚሰጠው ጉቦ እዚህ ውስጥ ይመደባል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ጉቦ መስጠት፣ መቀበል፣ አገናኝ መሆንና ተባባሪ መሆን በተሳሳተ ነገር ላይ መተባበር ስለሆነ ክልክል ነው።
  2. የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጉቦ ተቀባይንም ሆነ ሰጪን ስለረገሙ ጉቦ ከትላልቅ ወንጀሎች የሚመደብ ነው።
  3. ጉቦ በዳኝነትና ፍርድ ላይ ከሆነ የተከናወነው በውስጡ አላህ ካወረደው ፍርድ ውጪ በግፍ መፍረድም ስላለው ከባድ ወንጀልና አደገኛ ኃጢአት ይሆናል።
ተጨማሪ