+ -

عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رَضيَ اللهُ عنهُما أَنَّ رَسُولَ اللهِ صلى الله عليه وسلم:
نَهَى عَنْ كُلِّ ذِي نَابٍ مِنَ السِّبَاعِ، وَعَنْ كُلِّ ذِي مِخْلَبٍ مِنَ الطَّيْرِ.

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1934]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዓባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና:
ከሁሉም የክራንቻ ጥርስ ባለቤት አውሬና ከሁሉም ባለጥፍር በራሪ ስጋ (መብላትን) ከልክለዋል።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1934]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የማንኛውንም በክራንቻ ጥርሶቹ አማካይነት የሚያድን አውሬና የማንኛውንም በጥፍሩ የሚቆርጥና የሚይዝ የሆነ በራሪ ስጋውን ከመብላት ከለከሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ፈረንሳይኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. እስልምና በምግቦች፣ በመጠጦችና በሌሎችም ነገሮች ላይ ሁሉ ጥሩውን በመጠቀም ማነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. ክልክል መሆኑን ማስረጃ የጠቆመው ካልሆነ በቀር በምግብ ላይ መሰረቱ ፍቁድነት ነው።