+ -

عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا أَنَّهُ سَمِعَ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، يَقُولُ عَامَ الفَتْحِ وَهُوَ بِمَكَّةَ:
«إِنَّ اللَّهَ وَرَسُولَهُ حَرَّمَ بَيْعَ الخَمْرِ، وَالمَيْتَةِ وَالخِنْزِيرِ وَالأَصْنَامِ»، فَقِيلَ: يَا رَسُولَ اللَّهِ، أَرَأَيْتَ شُحُومَ المَيْتَةِ، فَإِنَّهَا يُطْلَى بِهَا السُّفُنُ، وَيُدْهَنُ بِهَا الجُلُودُ، وَيَسْتَصْبِحُ بِهَا النَّاسُ؟ فَقَالَ: «لاَ، هُوَ حَرَامٌ»، ثُمَّ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عِنْدَ ذَلِكَ: «قَاتَلَ اللَّهُ اليَهُودَ إِنَّ اللَّهَ لَمَّا حَرَّمَ شُحُومَهَا جَمَلُوهُ، ثُمَّ بَاعُوهُ، فَأَكَلُوا ثَمَنَهُ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 2236]
المزيــد ...

ከጃቢር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እርሱ የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መካ የተከፈተ ቀን መካ ውስጥ እንዲህ ሲሉ ሰማቸው:
"አላህና መልክተኛው አስካሪ መጠጥን፣ በክትን፣ አሳማንና ጣዖታትን ከመሸጥ ከልክለዋል።" ለርሳቸውም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! የበክት ሞራን በርሱ ጀልባዎቻችን ይለቀለቃሉ፣ ቆዳችንን እንቀባበታለን፣ ሰዎች በርሱ መብራትን በመስራት ይጠቀማሉ። ንገሩን እርሱም ክልክል ነውን?" ተባሉ። እርሳቸውም "በፍፁም እርሱም ክልክል ነው።" አሉና ቀጥለውም የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በዚህ ጊዜ እንዲህ አሉ "አላህ የሁዶችን ረገመ። አላህ ሞራን ከመጠቀም የከለከላቸው ጊዜ አሳምረው ሸጡትና የሸጡበትን ዋጋ በሉት።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 2236]

ትንታኔ

ጃቢር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መካ በተከፈተበት ዓመት መካ ሳሉ እንዲህ ሲሉ ሰማቸው "አላህና መልክተኛው አስካሪ መጠጥን፣ በክትን፣ አሳማንና ጣዖታትን ከመሸጥ ከልክለዋል።" ለርሳቸውም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! የበክት ሞራ መሸጥ ይፈቀድልናልን? ምክንያቱም በርሱ ጀልባዎቻችንን ይጠገኑበታል፣ ቆዳዎቻችንን እንቀባለን፣ ሰዎች በርሱ ኩራዞቻቸውን ያበሩበታል።" ተባሉ። እርሳቸውም "በፍፁም እርሱን መሸጥም ክልክል ነው።" አሉና ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ቀጠል አድርገው እንዲህም አሉ: "አላህ አይሁዶችን ይርገማቸው ያጠፋቸውና አላህ በነርሱ ላይ የእንስሳ ሞራን የከለከለ ጊዜ አቅልጠው ቅባቱን ሸጡትና ዋጋውን በሉት።"

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "በክት፣ አስካሪ መጠጥና አሳማ ሁሉ መሸጥ ሙስሊሞች ባጠቃላይ ክልክል መሆኑን ተስማምተውበታል።"
  2. ቃዲ እንዲህ ብለዋል: "በዚህ ሐዲሥ ውስጥ ከተጠቀሰው ሞራ መረዳት እንደሚቻለው መብላቱና መጠቀሙ የማይፈቀድ ነገር መሸጡም የሸጡበትን ዋጋ መብላቱም አይፈቀድም የሚለውን መርህ ከዚሁ ሐዲሥ የምንወስደው ቁምነገር ነው።"
  3. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «የሐዲሡ አመጣጥ የሚጠቁመው አብዛኞቹ እንደተረጎሙት "ክልክል ነው" ያሉት መሸጡን እንጂ መጠቀሙን እንዳልሆነ ነው።»
  4. ክልክልን ሐላል ለማድረግ የሚጠቀሙት ዘዴ ሁሉ ጥመት ነው።
  5. ነወዊ እንዲህ ብለዋል: «ዑለማዎች እንዲህ ብለዋል: የሞተን (በክትን) መሸጥ የመከልከሉ ጥቅል ውስጥ የካፊር ሬሳን የገደልነውና ከሀዲያን ሊገዙት ወይም ተለዋጭ መክፈል የፈለጉ ጊዜ የመሸጥ ክልክልነትን ያካትታል። በሌላ ሐዲሥ ውስጥ እንደመጣው ነውፈል ቢን ዐብደላህ አልመኽዙሚን የኸንደቅ ቀን ሙስሊሞች ገድለውት ከሀዲዎች ለሬሳው አስር ሺህ ዲርሃም ለነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አመጡ እርሳቸው ግን ሬሳውን ሰጥተዋቸው ገንዘቡን አልተቀበሉም።