+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَا مِنْ قَوْمٍ يَقُومُونَ مِنْ مَجْلِسٍ لَا يَذْكُرُونَ اللَّهَ فِيهِ إِلَّا قَامُوا عَنْ مِثْلِ جِيفَةِ حِمَارٍ، وَكَانَ لَهُمْ حَسْرَةً».

[صحيح] - [رواه أبو داود] - [سنن أبي داود: 4855]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"ሰዎች በውስጧ አላህን ያላወሱበትን መሰባሰብን (ጨርሰው) አይነሱም። የአህያ ሬሳ (በልተው) እንደሚሄዱ እና (በስብሰባው አላህን ባለማውሳታቸው) በእነርሱ ላይ ጸጸት (ቁጭትን) ቢሆንባቸው እንጂ።"

[ሶሒሕ ነው።] - [አቡዳውድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 4855]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በግማትና ቀፋፊነት በአህያ ጥንብ ላይ እንደተሰባበሱ ሰዎች አምሳያ ሆነው የሚነሱ እንጂ አንድ ስፍራ ላይ ተቀምጠው ከዚያም በዛ ስፍራ አላህን ሳያወሱበት የሚነሱ ሰዎች የሉም። ይህም አላህን ከማውሳት በወሬ ስለተጠመዱ ነው። የትንሳኤ ቀንም በዚህ አቀማመጣቸው ሰበብ በነርሱ ላይ ቁጭት፣ ጉድለትና ፀፀት እንደማይለቃቸው ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህን ከማውሳት በመዘናጋት ዙሪያ የተጠቀሰው ማስፈራሪያ በመቀመጫ ስፍራዎች ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም። ይልቁንም ሌሎችንም ሁኔታዎች ያጠቃልላል። ነወዊ እንዲህ ብለዋል "አንድ ስፍራ ላይ የተቀመጠ ሰው ያንን ስፍራ አላህን ሳያወሳበት መለየቱ ይጠላል።"
  2. የትንሳኤ ቀን እነርሱ የሚያጋጥማቸው ቁጭት ወይ ወቅቱን አላህን በማምለክ ሳይጠቀሙበት ምንዳና አጅር ስላመለጣቸው ነው። ወይም ደግሞ ወቅቱን አላህን በማመፅ ስላሳለፉት ወንጀል በመስራታቸውና በቅጣቱ ነው።
  3. ይህ ማስፈራሪያ የመጣው ይህ ዝንጉነት በሚፈቀዱ ነገሮች የተከሰተ ጊዜ ከሆነ ነው። በሀሜት፣ ሰውና ሰውን በማጣላትና ሌሎችም ክልክል የሆኑ ነገሮች የሚሰራባቸው ክልክል አቀማመጦችስ እንዴት ይሆኑ?!