+ -

عَنْ أَبِي عَبْسٍ عَبْدُ الرَّحْمَنِ بْنِ جَبْرٍ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«مَا اغْبَرَّتْ قَدَمَا عَبْدٍ فِي سَبِيلِ اللَّهِ فَتَمَسَّهُ النَّارُ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 2811]
المزيــد ...

ከአቢ ዐብስ ዐብዱራሕማን ቢን ጀብር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"በአላህ መንገድ ሲታገሉ አቧራ የለበሱ እግሮችን እሳት ልትነካቸው አትችልም።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 2811]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በአላህ መንገድ እየታገለ እግሮቹን አቧራ የነካው ሰው እሳት እንደማትነካው አበሰሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በአላህ መንገድ የሚታገል ሰው ከእሳት እንደዳነ መበሰሩን እንረዳለን።
  2. አቧራው ሰውነትን ባጠቃላይ የሚያዳርስ ከመሆኑም ጋር እግር ተለይቶ የተወሳበት ምክንያት በዛ ዘመን የነበሩት አብዛኛዎቹ ሙጃሂዶች እግረኞች ስለነበሩና በማንኛውም ሁኔታ እግርን አቧራ መንካቱ የማይቀር ስለሆነ ነው።
  3. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «አቧራ እግርን መንካቱ ብቻ እሳትን እርም የሚያደርግላት ከሆነ የለፋ፣ አቅሙን የሰጠና በሙሉ ችሎታው የታገለ ሰውስ እንዴት ሊመነዳ ይሆን?»