عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بن مسعودٍ رضي الله عنه قَالَ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«إِنَّ مِنْ شِرَارِ النَّاسِ مَنْ تُدْرِكُهُ السَّاعَةُ وَهُمْ أَحْيَاءٌ، وَمَنْ يَتَّخِذُ الْقُبُورَ مَسَاجِدَ».

[حسن] - [رواه أحمد]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ:
‹ከሰዎች ሁሉ መጥፎዎቹ እነሱ በህይወት እያሉ ሰአቲቷ (ቂያማ) የምታገኛቸውና መቃብሮችን መስገጃ አድርገው የሚይዙት ናቸው።›"

Hasan/Sound. - [Ahmad]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ስለ መጥፎ ሰዎች ተናገሩ። እነርሱም በህይወት ሳሉ ሰአቲቱ (ቂያማ) የምትቆምባቸውና እነዚያ መቃብሮችን መስገጃ አድርገው በመያዝ እርሱ ዘንድና ወደርሱ በመዞር የሚሰግዱት ናቸው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወደ ሺርክ ስለሚያዳርስ መቃብሮች ላይ መስገጃ መገንባት ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. መስጂድ ማለት ባይገነባበት እንኳ የሚሰገድበትን ስፍራ የሚጠቁም ስያሜ ስለሆነ ባይገነባበት እንኳ መቃብር ዘንድ መስገድ ክልክል ነው።
  3. የደጋጎችን መቃብር ለሶላት መስገጃነት የያዘ ሰው ወደ አላህ መቃረብን አስቦ እንደሆነ ቢሞግት እንኳ ከሰዎች ሁሉ መጥፎ ነው።