عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعت النبي صلى الله عليه وسلم يقول:
«مَنْ حَجَّ لِلهِ فَلَمْ يَرْفُثْ وَلَمْ يَفْسُقْ رَجَعَ كَيَوْمِ وَلَدَتْهُ أُمُّهُ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንደተላለፈው፡ ነብዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ ብሏል፡
"ሚስቱን ሳይገናኝ እንዲሁም ሳያምፅ ለአሏህ ሓጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እርሱን እንደወለደችበት ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ሚስቱን ሳይገናኝ - "ረፈሥ" የሚለው ቃል ፆታዊ ግንኙነትንም ይሁን መሳሳምና መተሻሸትን የመሰሉ የግንኙነት መንደርደሪያዎችን እንዲሁም ፀያፍ የቃል አጠቃቀምንም የሚያጠቃልል ቃል ነው። ወንጀልና ሀጢአት በመፈፀም - ሳያምፅ ‐ ሓጅን ያከናወነ ያለውን ደረጃ ገለፁ። ማመፅ ውስጥ ከሚጠቃለሉት መካከል በኢሕራም ጊዜ የተከለከለን ማድረግ ይገኝበታል። በዚህ መልኩ ሓጅን ያከናወነ ሰው ልክ ህፃን ልጅ ከወንጀል የፀዳ ሆኖ እንደሚወለደው እርሱም ከወንጀሉ የተማረ ሆኖ ከሓጅ ይመለሳል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወንጀል ምንም እንኳ በማንኛውም ሁኔታ የተከለከለ ቢሆንም በሓጅ ስርአት ግን የሀጅን የአምልኮ ስርአት ለማላቅ ሲባል ክልክልነቱ የበረታ እንደሚሆን፤
  2. የሰው ልጅ ሲወለድ ከወንጀል የፀዳ ሆኖ የሚወለድ በመሆኑ የሌላ ወንጀል የሚጫንበት እንዳልሆነ፤
ተጨማሪ