+ -

عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ سَمُرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لَا تَحْلِفُوا بِالطَّوَاغِي، وَلَا بِآبَائِكُمْ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1648]
المزيــد ...

ከዐብዲረሕማን ቢን ሰሙራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"በጣዖታትም ሆነ በአባቶቻችሁ አትማሉ።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1648]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አጋርያኖች ከአላህ ውጪ ያመልኳቸው በነበሩትና ለክህደታቸውና ጥመታቸው ምክንያት በነበሩት ጣዖታት ከመማል ከለከሉ። በድንቁርና ዘመን የዐረቦች ልማድ ከነበሩት ነገሮች መካከል ለመኩራራትና ለማላቅ በአባቶቻቸው መማል ነበርና ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በአባቶች ከመማልም ከለከሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በአላህ፣ በስሞቹና በባህሪያቱ ካልሆነ በቀር መማል አይፈቀድም።
  2. በጣዖታት፣ በአባት፣ በመሪዎችና በመሳሰሉት በሁሉም ውድቅ በሆኑ ነገሮች መማል መከልከሉን እንረዳለን።
  3. መማል በአላህ ካልሆነ ከትንሹ ሽርክ መካከል ነው። የሚማልበትን አካል በቀልቡ ውስጥ እያላቀው ከሆነ የሚምለው አላህ እንደሚላቀው ካላቀው ወይም ለርሱ አንዳች አምልኮ ይገባዋል ብሎ ካመነ ትልቁ ሽርክ ይሆናል።