عَنْ عُبَادَةَ بْنِ الصَّامِتِ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَا صَلَاةَ لِمَنْ لَمْ يَقْرَأْ بِفَاتِحَةِ الكِتَابِ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 756]
المزيــد ...

ከዑባዳህ ቢን ሷሚት (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"የመጽሐፉን መክፈቻ (ፋቲሓን) ያላነበበ ሰው ሶላት የለውም።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 756]

ማብራሪያ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የፋቲሓን ምዕራፍ በመቅራት ካልሆነ በቀር ሶላት ትክክለኛ እንደማትሆን ገለፁ። ፋቲሓ በሁሉም ረከዓዎች ከሚደረጉ የሶላት ማእዘናት መካከል አንዷ ናት።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. ፋቲሓን መቅራት እየቻለ ፋቲሓን ከመቅራት ፋንታ ሌላ ምእራፍ መቅራት አያብቃቃም።
  2. አውቆም ሆነ ሳያውቅ ወይም ረስቶ ፋቲሓ ያልተቀራበት ረከዓ የተበላሸ መሆኑን እንረዳለን። ምክንያቱም ፋቲሓ የሶላት ማእዘን ናት። ማእዘን ደግሞ በማንኛውም ሁኔታ ላይ ቢሆን አይወድቅም።
  3. ተከታይ የሆነ ሰው ኢማሙን ሩኩዕ ላይ ቢደርስበት ፋቲሓን የመቅራት ግዴታው ይነሳለታል።
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (56)