عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ عَنْ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنَّهُ قَالَ:
«سَيَكُونُ فِي آخِرِ أُمَّتِي أُنَاسٌ يُحَدِّثُونَكُمْ مَا لَمْ تَسْمَعُوا أَنْتُمْ وَلَا آبَاؤُكُمْ، فَإِيَّاكُمْ وَإِيَّاهُمْ».
[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
"በመጨረሻዎቹ ሕዝቦቼ (ኡመቴ) ውስጥ እናንተም ሆነ አባቶቻችሁ ያልሰማችሁትን የሚነግሯችሁ ሰዎች ይመጣሉ። አደራችሁን አደራችሁን ተጠንቀቋቸው።"
Sahih/Authentic. - [Muslim]
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመጨረሻዎቹ ኡመታቸው ውስጥ ውሸትን የሚቀጥፉ ሰዎች ብቅ እንደሚሉ ተናገሩ። ከነርሱ በፊት አንድም ሰው ያልተናገረውን ይናገራሉ፤ የተዋሹና የተቀጠፉ ሐዲሦችን ይናገራሉ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከነርሱ እንድንርቅና እንዳንቀማመጣቸው፣ ከርሱ መራቅ እስኪያቅተን ድረስ ይህ የተቀጠፈ (የተፈበረከ) ሐዲሥ ነፍስ ውስጥ ተፅዕኖ እንዳያሳድርብንም ሐዲሣቸውን አለመስማትን አዘዙን።