+ -

عَنْ سَمُرَةَ بْنِ جُنْدَبٍ وَالْمُغِيرَةِ بْنِ شُعْبَةَ رضي الله عنهما قَالَا: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَنْ حَدَّثَ عَنِّي بِحَدِيثٍ يُرَى أَنَّهُ كَذِبٌ، فَهُوَ أَحَدُ الْكَاذِبِينَ».

[صحيح] - [رواه مسلم في مقدمته]
المزيــد ...

ከሰሙራ ቢን ጁንዱብና ሙጚራ ቢን ሹዕባ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ውሸት መሆኑን እያወቀ ከኔ አንድ ሐዲሥን ያወራ ሰው ከውሸታሞች አንዱ ነው።"»

[ሶሒሕ ነው።] - - [ሶሒሕ ሙስሊም]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በርሳቸው ላይ እየዋሸ እንደሆነ እያወቀ ወይም እየተጠራጠረ ወይም በአብዛኛው ግምቱ እየዋሸ እንደሆነ እየተሰማው ከርሳቸው ንግግርን ያስተላለፈና ያወራ ሰው ይህንን ውሸት ለመጀመሪያ ጊዜ ከቀጠፈው ጋር (በወንጀሉ) ይጋራል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية الرومانية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የተወሩን ሐዲሦች ማረጋገጥና ከማውራት በፊት ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባ እንረዳለን።
  2. የውሸታምነት ባህሪ ውሸትን በፈጠረ ሁሉ ላይ፣ በማስተላለፉ በተሳተፈ ላይና በሰዎች መካከል ያሰራጨውም ሁሉ ይገለፅበታል።
  3. የተፈበረከ ሐዲሥ መሆኑን ባወቀ ሰው ወይም የተፈበረከ መሆኑን ጥርጣሬው ባመዘነ ሰው ላይ ለማስጠንቀቅ ካልሆነ በቀር የተፈበረከ ሐዲሥን ማውራት አይፈቀድም።