+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«اثْنَتَانِ فِي النَّاسِ هُمَا بِهِمْ كُفْرٌ: الطَّعْنُ فِي النَّسَبِ، وَالنِّيَاحَةُ عَلَى الْمَيِّتِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 67]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"በሰዎች ውስጥ ሁለት ነገሮች አሉ፤ ክህደት ናቸው። በዘር መተቸትና በሞተ ላይ ሙሾ ማውረድ ናቸው።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 67]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በሰዎች መካከል ስለሚገኙ ሁለት የከሃዲያን ስራዎችና የድንቁርና ዘመን ስነ ምግባሮች ተናገሩ። እነርሱም:
የመጀመሪያው: ሰዎችን በዘራቸው መተቸት፣ ማሳነስና በዘር እነርሱ ላይ መኩራራት ነው።
ሁለተኛው: በመከራ ወቅት የአላህን ውሳኔ በማማረር ድምፅን ከፍ ማድረግ ወይም ከትእግስት ማጣት ብዛት ልብስን መቅደድ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በመተናነስ ላይና በሰዎች ላይ አለመኩራት መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. በመከራ ላይ መታገስና አለመበሳጨት ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
  3. እነዚህ ተግባራት ከትንሹ ክህደት ነው የሚመደቡት። ከትንሹ ክህደት ክፍሎች መካከል አንድ ስራን የሰራ ሰው ደሞ ትልቁን ክህደት እስኪሰራ ድረስ ከእስልምና የሚያስወጣ ክህደትን የካደ አይሆንም።
  4. እስልምና ዘር መተቻቸትና የመሳሰሉትን በሙስሊሞች መካከል መከፋፈልን የሚፈጥሩ ነገሮችን ሁሉ ከልክሏል።
ተጨማሪ