+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَنْ حَلَفَ فَقَالَ فِي حَلِفِهِ: وَاللَّاتِ وَالعُزَّى، فَلْيَقُلْ: لاَ إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَمَنْ قَالَ لِصَاحِبِهِ: تَعَالَ أُقَامِرْكَ، فَلْيَتَصَدَّقْ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 4860]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"የማለ ሰው በመሀላውም 'በላትና ዑዛ እምላለሁ' ያለ ሰው 'ላኢላሃ ኢለሏህ' ይበል። ለባልደረባው 'ና ቁማር እንጫወት' ያለ ሰውም ይመፅውት።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 4860]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአላህ ውጪ ከመማል አስጠነቀቁ። አማኝ የሆነ ሰው ከአላህ በቀር በማንም አይምልምና። ከአላህ ውጪ የማለና ለምሳሌ በላት፣ በዑዛ የማለ ሰው (እነዚህ ሁለቱ ከእስልምና በፊት በድንቁርና ዘመን ይመለኩ የነበሩ ጣዖታት ናቸው።) ነፍሱን ለማዳን ከሽርክ ለመፅዳትና ለዛ መሀላው ማካካሻ እንዲሆነው አስከትሎ "ላኢላሃ ኢለሏህ" የማለት ግዴታ እንዳለበት ተናገሩ።
ቀጥለውም ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለባልደረባው "ና ቁማር እንጫወት" ያለ ሰው (ቁማር ማለት ሁለት ወይም ከዛ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸው አሸናፊው የሚወስደው ገንዘብ መድበው ለመሸናነፍ መጫወት ነው። ከመካከላቸውም እያንዳንዳቸው ወይ ያተርፋል ወይ ይከፍላል።) የጠራበትን ወንጀል ለማካካስ አንዳች ነገር መመፅወቱ እንደሚወደድለት ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. መሀላ በአላህ፣ በስሞቹና በባህሪያቱ ካልሆነ በቀር አይሆንም።
  2. ከአላህ ውጪ መማል ክልክል ነው። ይህም እንደላትና ዑዛ በመሰሉ በጣዖታትም ማለ ወይም በታማኝነት ማለ ወይም በነቢዩ ማለ ወይም ከዚህ ውጪ ባሉም ቢምል ተመሳሳይ ነው።
  3. ኸጧቢ እንዲህ ብለዋል: «መሀላ የሚፈፀመው ታላቅ ተመላኪ በሆነ ብቻ ነው። በላትና በመሳሰሉት የማለ ጊዜ ከሃዲያን ጋር ተጠጋግቷል። ስለዚህም የተውሒድን ቃል እንዲያክል ታዘዘ።»
  4. ከአላህ ውጪ በማለ ሰው ላይ የመሀላ ማካካሻ የለበትም። ያለበት ግዴታ ተውበትና ምህረትን መጠየቅ ነው። ይህም ከተውበት ውጪ ምንም ሊያስምረው የማይችል ትልቅ ወንጀል ስለሆነ ነው።
  5. በሁሉም ቅርፁና ይዘቱ ቁማር ክልክል መሆኑን እንረዳለን። ይህም አላህ ከአስካሪ መጠጥና ከጣዖት አምልኮ ጋር አቆራኝቶ የከለከለው ቁማር ነው።
  6. ወንጀልን ከፈፀሙ በኋላ ከወንጀሉ መመለስ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
  7. ኃጢዐት ላይ የወደቀ ሰው መልካም ስራን ሊያስከትልላት ይገባል። መልካም ስራዎች ኃጢአቶችን ያስወግዳሉና።