عَنْ عَائِشَةَ رضي الله عنها قَالَتْ:
كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَسْتَحِبُّ الْجَوَامِعَ مِنَ الدُّعَاءِ، وَيَدَعُ مَا سِوَى ذَلِكَ.

[صحيح] - [رواه أبو داود وأحمد] - [سنن أبي داود: 1482]
المزيــد ...

ከምእመናን እናት ዓኢሻ -አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው እንዲህ ብላለች፦
"የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ጠቅለል ያሉ ዱዓዎችን ማድረግ ይወዱ ነበር። ከዚህ ውጪ ያለውንም ይተዉ ነበር።"

[ሶሒሕ ነው።] - [አቡዳውድና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 1482]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የዱንያንም ሆነ የመጪውን አለም መልካም ነገር የጠቀለለ አላህ ላይ ማወደስና መልካም ፍላጎቶችንም ያካተተ ሁኖ ቃሉ አንሶ ሀሳቡ የበዛ ዱዓን ማድረግ ይወዱ ነበር። ከዚህ ውጪ ያለንም ይተዉ ነበር።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዱዓን በጥቂትና በርካታ ሀሳቦችን በሰበሰቡ ቃላቶች ማድረግ እንደሚወደድ፤ ዱዓ ላይ የቃላት ስንጠቃና ከአቅም በላይ መጣጣርም እንደሚጠላ የነቢዩንም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) መመሪያ መቃረን ነው።
  2. የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በጠቅላይ ቃላቶች ተለይተዋል።
  3. ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ዱዓ እንዳደረጉበት የተረጋገጡ ዱዓዎች ላይ ቢረዝምና ቃሉ ቢበዛ እንኳ ያንን ዱዓ ማድረግ ላይ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ተረድተናል።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (43)