+ -

عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«إِنَّ أَهْوَنَ أَهْلِ النَّارِ عَذَابًا مَنْ لَهُ نَعْلَانِ وَشِرَاكَانِ مِنْ نَارٍ، يَغْلِي مِنْهُمَا دِمَاغُهُ كَمَا يَغْلِ الْمِرْجَلُ، مَا يَرَى أَنَّ أَحَدًا أَشَدُّ مِنْهُ عَذَابًا، وَإِنَّهُ لَأَهْوَنُهُمْ عَذَابًا».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 213]
المزيــد ...

ከኑዕማን ቢን በሺር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦
"ከጀሀነም ነዋሪዎች መካከል እጅግ ዝቅተኛ ቅጣት የሚቀጣው ለርሱ ሁለት የእሳት ጫማዎችና የጫማ ማሰሪያዎች የሚደረግለት ነው። በነርሱም ምክንያት ድስጥ እንደሚንፈቀፈቀው አንጎሉ ይንፈቀፈቃል። ከርሱ የበለጠ ቅጣት የሚቀጣ አንድም ሰው አለ ብሎም አያስብም። እርሱ እየተቀጣ ያለው ግን እጅግ ዝቅተኛውን ቅጣት ነው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 213]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የትንሳኤ ቀን እጅግ ዝቅተኛ ቅጣት የሚቀጣው የእሳት ነዋሪ ለርሱ ሁለት የእሳት ጫማዎችና ማሰሪያዎች የሚደረግለት ሰው እንደሆነና ከአቃጣይነታቸው የተነሳ የነሃስ ድስጥ እንደሚንፈቀፈቀው አንጎሉም የሚንፈቀፈቅ መሆኑን፤ ከርሱ የበለጠ የሚቀጣ አንድም ሰው አለ ብሎም እንደማያስብ፤ እርሱ ግን እጅግ ዝቅተኛውን ቅጣት የሚቀጣ ነው መሆኑን ተናገሩ። ይህንን የሚያስበውም አካላዊ ቅጣቱ ከመንፈሳዊ ቅጣቱ ጋር በጋራ እንዲቀጣበት ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከሃዲያንና ወንጀለኞች ከዚህ የእሳት ውስጥ የቅጣት ጭንቀት መጠንቀቅ እንዳለባቸው እንረዳለን። ይህም ይህን ከሚያስከትልባቸው ነገር እንዲርቁ ነው።
  2. እሳት የሚገቡ ሰዎች ደረጃ እንደየ መጥፎ ስራቸው መጠን እንደሚለያይ እንረዳለን።
  3. አላህ ከርሷ ነፃ ያውጣንና የእሳት ቅጣት ከባድነትን እንረዳለን።