+ -

عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لَمَّا عُرِجَ بِي مَرَرْتُ بِقَوْمٍ لَهُمْ أَظْفَارٌ مِنْ نُحَاسٍ يَخْمُشُونَ بها وُجُوهَهُمْ وَصُدُورَهُمْ، فَقُلْتُ: مَنْ هَؤُلَاءِ يَا جِبْرِيلُ، قَالَ: هَؤُلَاءِ الَّذِينَ يَأْكُلُونَ لُحُومَ النَّاسِ، وَيَقَعُونَ فِي أَعْرَاضِهِمْ».

[حسن] - [رواه أبو داود] - [سنن أبي داود: 4878]
المزيــد ...

አነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዳስተላለፉት እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
«ወደ ሰማይ እንዳርግ በተደረግኩበት ወቅት የነሃስ ጥፍር ባላቸውና በነዛም ጥፍሮች ፊቶቻቸውንና ደረቶቻቸውን በሚቧጭሩ ሰዎች በኩል አለፍኩ። እኔም "ጂብሪል ሆይ! እነዚህ እነማን ናቸው?" ብዬ ጠየቅኩት። እርሱም "እነዚህ የሰዎችን ስጋ የሚበሉና የሰዎችን ክብር የሚያጎድፉ ናቸው።" በማለት መለሰልኝ።»

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ ዘግበውታል። - አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 4878]

ትንታኔ

ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - በኢስራእና ሚዕራጅ ምሽት ወደ ሰማይ በወጡበት ወቅት የነሃስ ጥፍሮች ባሏቸውና ፊቶቻቸውንና ደረቶቻቸውንም በሚቧጭሩና በሚቦጭቁ ሰዎች በኩል እንዳለፉ ተናገሩ። ነቢዩም - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ጂብሪልን ዐለይሂ ሰላም እነዚህ ሰዎች በዚህ ቅጣት እንዲመነዱ ያደረጋቸው ምንድነው? ብለው ጠየቁት። ጂብሪልም ዐለይሂ ሰላም እነዚህ ሰዎችን የሚያሙና ያለአግባብ ስለሰዎች ክብር የሚናገሩ ናቸው። ብሎ መለሰላቸው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሃሜትን በማስመልከት ከባድ ማስጠንቀቂያ መምጣቱንና የሚያማ ሰው የሰውን ስጋ ከመብላት ጋር እንደተመሳሰለ እንረዳለን።
  2. በሃሜትና በመሳሰሉት የሰዎችን ክብር መንካት ከትላልቅ ወንጀሎች እንደሆነ እንረዳለን።
  3. ጢቢይ "የሚቧጭሩ" በሚለው የሐዲሡ ቃል ዙሪያ እንዲህ ብለዋል: "ፊትንና ደረትን መቧጨር የሙሾ አውራጅ ሴቶች ባህሪ ከመሆኑ አንፃር የሙስሊሞችን ክብር ለሚያጎድፉ ሰዎችም መቀጫቸው ያንኑ ባህሪ መላበስ አደረገው። ይህም ሁለቱም ባህሪያት የወንዶች ሳይሆኑ የሴቶች ለዛውም በአስቀያሚ ሁኔታና በመጥፎ ገፅታ ላይ ሲሆኑ የሚላበሱት ባህሪ እንደሆነ የሚገልፅ ነው።"
  4. በሩቅ እውቀትና አላህና መልክተኛው - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - በተናገሩት ባጠቃላይ ማመን ግዴታ እንደሆነ እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ