عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«صِنْفَانِ مِنْ أَهْلِ النَّارِ لَمْ أَرَهُمَا، قَوْمٌ مَعَهُمْ سِيَاطٌ كَأَذْنَابِ الْبَقَرِ يَضْرِبُونَ بِهَا النَّاسَ، وَنِسَاءٌ كَاسِيَاتٌ عَارِيَاتٌ مُمِيلَاتٌ مَائِلَاتٌ، رُؤُوسُهُنَّ كَأَسْنِمَةِ الْبُخْتِ الْمَائِلَةِ، لَا يَدْخُلْنَ الْجَنَّةَ، وَلَا يَجِدْنَ رِيحَهَا، وَإِنَّ رِيحَهَا لَيُوجَدُ مِنْ مَسِيرَةِ كَذَا وَكَذَا».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
'አሁን ላይ እኔ ያላየኋቸው ሁለት አይነት የእሳት ባለቤቶች አሉ። (እነሱም) ሰዎችን የሚደበድቡበት እንደከብት ጭራ የመሰለ አለንጋ ያላቸው ሰዎች እና ለብሰው የተራቆቱ የሆኑ ራሳቸው ተዘንብለው ሌሎችን ለክፉ የሚጋብዙ፤ ጭንቅላታቸው እንደተዘነበለ የግመል ሻኛ የሆነ ሴቶች ናቸው። እነዚህ ጀነት አይገቡም፤ መዓዛዋንም አያገኙም። የጀነት ሽታዋም (እነሱ ካሉበት) የሆነ ያክል ርቆ ይገኛል።'"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሁለት አይነት ሰዎች የእሳት ባለቤቶች እንደሆኑና በሳቸው ዘመን እንዳላዩዋቸውና እንደሌሉ፤ በተቃራኒው ከርሳቸው ህልፈት በኋላ እንደሚመጡ ተናገሩ።
የመጀመሪያው አይነት ሰዎች: ሰዎችን የሚመቱበት የከብት ጭራ የሚያክል አለንጋ ይዘው የሚዞሩ ሰዎች ናቸው። እነርሱም ሰዎችን ያለ አግባብ በመምታት የግፈኞች ተባባሪ የሆኑ ፖሊሶች ናቸው።
ሁለተኛው አይነት ሰዎች ደግሞ: በተለምዶ የሴቶች ተፈጥሮ የሆነውን የጥብቅነትንና አይነ አፋርነትን ልብስ ያወለቁ ሴቶች ናቸው።
በተጨባጭ ገላቸው ላይ ልብስ ያለ ቢሆንም በትክክለኛው ግን የተራቆቱ ናቸው። ምክንያቱም እነሱ ቆዳቸውን ግልፅ ለማውጣት ሰውነትን የሚያሳይ ቀጭን ልብስ ነውና የሚለብሱት፤ (ወይ) ውበታቸውን ለማጉላት የተወሰነ ሰውነታቸውን ሸፍነው የተወሰነውን የገለጡ ናቸውና በማለት እነዚህን ሴቶች ገለጿቸው። በአለባበሳቸውና በአረማመዳቸው የወንዶችን ቀልብ ወደነርሱ እንዲያዘነብል የሚያደርጉ፣ ትከሻዎቻቸውንም የሚያወዛውዙ፣ ሌሎችንም እነርሱ ወደ ወደቁበት ጥመት እንዲያዘነብሉ የሚያደርጉ ናቸው። ከነዚህ ሴቶች ባህሪ መካከልም: ጭንቅላታቸው ያዘነበለ የግመል ሻኛ ይመስላል። የፀጉራቸውን መጠን በማሰሪያና በመሳሰሉት በማሰር ያተልቋታል። በግመል ሻኛ የተመሳሰሉት ፀጉራቸውና ጉንጉናቸው ከጭንቅላታቸው በላይ ከፍ ስለሚልና የግመል ሻኛ እንደሚዘነበለው ፀጉራቸውን በሚጎነጎኑት ሳቢያ ወደአንድ ጎን እስኪዘነበል ድረስ ሰበር ስለሚል ነው። ይህን ባህሪ የተላበሱ ሴቶች እነርሱ ላይ ይህ ከባድ ዛቻ አለባቸው። እርሱም ጀነት ላይገቡ፣ ሽታዋንም ላያገኙ፣ ወደርሷም ላይቀርቡ ነው። የጀነት መዓዛ ከሩቅ ስፍራ ነው የሚሸተው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሰዎችን ወንጀል ሳይሰሩ ወይም ኃጢአት ሳይተገብሩ መምታትና ማወክ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. ግፈኞችን በግፋቸው ላይ ማገዝ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  3. ሴቶች ከመገላለጥ፣ ከመራቆት፣ ሀፍረተ ገላን ከሚገልፅ ወይም ቅርፅን ከሚያሳይ ጠባብና ስስ ልብስ መጠንቀቅ እንዳለባቸው።
  4. ሙስሊም ሴቶች የአላህን ትእዛዝ አጥብቀው በመያዝ ላይና አላህን ከሚያስቆጣውና በመጨረሻው ዓለም አሳማሚና ዘውታሪ ቅጣት እንዲገባቸው ከሚያደርጓቸው ነገር እንዲርቁ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  5. ይህ ሐዲሥ የነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ነቢይነት ከሚጠቁሙ ሐዲሦች አንዱ ነው። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) (በህይወት ዘመናቸው) ያልተከሰተ ሩቅ ጉዳይን ተናገሩ እንደተናገሩትም ተከሰተ።