عَنْ عُقْبَةَ بْنِ عَامِرٍ الْجُهَنِيِّ رضي الله عنه:
أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَقْبَلَ إِلَيْهِ رَهْطٌ، فَبَايَعَ تِسْعَةً وَأَمْسَكَ عَنْ وَاحِدٍ، فَقَالُوا: يَا رَسُولَ اللهِ، بَايَعْتَ تِسْعَةً وَتَرَكْتَ هَذَا؟ قَالَ: «إِنَّ عَلَيْهِ تَمِيمَةً»، فَأَدْخَلَ يَدَهُ فَقَطَعَهَا، فَبَايَعَهُ، وَقَالَ: «مَنْ عَلَّقَ تَمِيمَةً فَقَدْ أَشْرَكَ».

[حسن] - [رواه أحمد]
المزيــد ...

ከዑቅባህ ቢን ዓሚር አልጁሀኒይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- እንደተላለፈው፦
"ወደ አላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የተወሰኑ ሰዎች መጡ። ከዘጠኙ ጋር ቃልኪዳን ተጋቡና ከአንዱ ጋር ቃልኪዳን ከመጋባት ተቆጠቡ። ሶሐቦችም 'የአላህ መልክተኛ ሆይ! ከዘጠኙ ጋር ቃልኪዳን ተጋብተው ይህንን ለምን ተዉ?' አሉ። እርሳቸውም 'እርሱ ላይ ሒርዝ ስላለ ነው።' አሉ። (ይህንን ሲሰማ) እጁን አስገባና ቆረጠው። እርሳቸውም ቃልኪዳን ተጋቡትና 'ሒርዝ ያንጠለጠለ ሰው በርግጥም አጋርቷል!' አሉ።"

Sahih/Authentic. - [Ahmad]

ትንታኔ

የተወሰኑ ጭፍሮች ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መጡ። ብዛታቸውም አስር ነበሩ። ከነርሱ መካከል ከዘጠኙ ጋር በኢስላም ላይና እርሳቸውን በመከተል ላይ ቃል ተጋቡና ከአስረኛው ጋር ቃልኪዳን ሳይጋቡ ቀሩ። የዚህን ምክንያት የተጠየቁ ጊዜም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ: እርሱ ላይ ሒርዝ አለበት። (ሒርዝ) ማለት፦ ዓይንን ወይም ጉዳትን ለመከላከል ከጨሌና ከሌላም ነገር የሚሰራ የሚታሰር ወይም የሚንጠለጠል ነው። ሰውዬውም ወደ ሒርዙ ስፍራ እጁን ከቶ በመቁረጥ ከሒርዙ ጠራ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የዚህ ጊዜ ቃልኪዳን ተጋቡት። ከሒርዝ ለማስጠንቀቅና ብይኗን ለመግለፅም እንዲህ አሉ: "ሒርዝ ያንጠለጠለ ሰው በርግጥም አጋርቷል።"

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከአላህ ውጪ በሆነ ላይ የተመካን ሰው አላህ ጉዳዩን ካሰበው በተቃራኒ ያደርግበታል።
  2. ጉዳትንና ዐይንን ለመከላከል ሒርዝ ማንጠልጠል ሰበብ ይሆናል ብሎ ማመን ትንሹ ሺርክ ነው። በራሷ ትጠቅማለች ብሎ ካመነ ግን ትልቁ ሺርክ ነው የሚሆነው።