عَنْ أَبِي بُرْدَةَ، عَنْ أَبِيهِ أَبِي مُوسَى الأَشْعَريِّ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ:
أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ بَعَثَهُ إِلَى اليَمَنِ، فَسَأَلَهُ عَنْ أَشْرِبَةٍ تُصْنَعُ بِهَا، فَقَالَ: وَمَا هِيَ؟، قَالَ: «البِتْعُ وَالمِزْرُ»، فَقِيلَ لِأَبِي بُرْدَةَ: مَا البِتْعُ؟ قَالَ: نَبِيذُ العَسَلِ، وَالمِزْرُ: نَبِيذُ الشَّعِيرِ، فَقَالَ: «كُلُّ مُسْكِرٍ حَرَامٌ» خرجه البخاري.
وَخَرَّجَهُ مُسْلِمٌ وَلَفْظُهُ: قَالَ: بَعَثَنِي رَسُولُ اَلله أَنَا وَمُعَاذٌ إِلَى اَليَمَنِ، فَقُلْتُ: يَا رَسُولُ اَللَّهِ! إِنَّ شَرَابًا يُصْنَعُ بِأَرْضِنَا يُقَال لَهُ: المِزَرُ مِنَ الشَّعِيرِ، وَشَرَابٌ يُقَالُ لَهُ: البِتْعُ مِنَ العَسَلِ، فَقَالَ: «كُلُّ مُسْكِرٍ حَرَامٌ».
وَفِي رِوَايَةٍ لِمُسْلِمٍ: «فَقَالَ: كُلُّ مَا أَسْكَرَ عَنِ الصَّلَاةِ فَهُوَ حَرَامٌ».
وَفِي رِوَايَةٍ لَهُ: «وَكَانَ رَسُولُ الله قَدْ أُعْطِيَ جَوَامِعَ الكَلِمِ بِخَوَاتِمِهِ، فَقَالَ: أَنْهَى عَنْ كُلِّ مُسْكِرٍ أَسْكَرَ عَنْ الصَّلَاةِ».
[صحيح] - [رواه البخاري ومسلم] - [الأربعون النووية: 46]
المزيــد ...
ከአቡ ቡርዳህ እንደተላለፈው: እርሳቸው ከአባታቸው አቡ ሙሳ አልአሽዓሪይ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዳስተላለፉት አቡ ሙሳ እንዲህ አሉ:
«ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ወደ የመን ላኩት። በየመን ውስጥ ይሰራ ስለነበር መጠጥም ጠየቃቸው። እርሳቸውም "ምንድናት?" አሉት። እርሱም: "ቢትዕ እና ሚዝር ናቸው።" አላቸው። (ሐዲሡን እያስተላለፈ ላለው) ለአቡ ቡርዳ "ቢትዕ ምንድን ነው?" ተብሎ ተጠየቀ። እርሱም "በማር የሚሰራ አስካሪ መጠጥ ነው።" አላቸው። "ሚዝርስ?" ብለው ሲጠይቁት "በገብስ የሚሰራ አስካሪ መጠጥ ነው።" ብሎ መለሰላቸው። ነቢዩም "ሁሉም አስካሪ ነገር ሐራም ነው።" ብለው መለሱለት።» ሙስሊም ዘግበውታል። የሙስሊም ዘገባውም: «አቡ ሙሳ አልአሽዓሪይ እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ እኔና ሙዓዝን ወደ የመን ላኩን።" እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በሃገራችን ከገብስ የሚሰራ ሚዝር የሚባልና ከማር የሚሰራ ቢትዕ የሚባል አስካሪ መጠጥ አለ።" አልኩኝ። እርሳቸውም "ሁሉም አስካሪ ሐራም ነው።" በማለት መለሱ።» በሌላ የሙስሊም ዘገባም «ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉ: ሁሉም ከሶላት ያሰከረ ነገር ሁሉ ሐራም ነው።» በሌላ የሙስሊም ዘገባም: «የአላህ መልክተኛ ሀሳብን ጠቅልሎ የመናገርና የማጠቃለል ተሰጥዖ የተሰጣቸው ነበሩ። እንዲህ አሉ: ከሶላት ካሰከረ ከሁሉም አስካሪ ነገር እከለክላለሁ።»
[ሶሒሕ ነው።] - [رواه البخاري ومسلم] - [الأربعون النووية - 46]
አቡ ሙሳ አልአሽዓሪይ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተናገሩት: ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ወደ የመን ላኩት። በየመን መሬት ስለሚሰራ መጠጥ ክልክል ስለመሆኑ ጠየቃቸው። ነቢዩም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ስለመጠጡ ምንነት ዝርዝር ጉዳይ ጠየቁት። አቡ ሙሳም - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - "ቢትዕ ከማር የሚሰራ አስካሪ መጠጥ ሲሆን ሚዝር ደሞ ከገብስ የሚሰራ አስካሪ መጠጥ ነው።" ብለው ተናገሩ። ነቢዩም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ንግግርን ሰብስቦ የመናገር ተሰጥዖ ተሰጥቷቸዋልና "ሁሉም አስካሪ ሐራም ነው።" አሉት።