ምድቡ:
+ -

عَنْ أَبِي مُحَمَّدٍ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو بْنِ العَاصِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لَا يُؤْمِنُ أَحَدُكُمْ حَتَّى يَكُونَ هَوَاهُ تَبَعًا لِمَا جِئْتُ بِهِ».

[قال النووي: حديث صحيح] - [رويناه في كتاب الحجة بإسناد صحيح] - [الأربعون النووية: 41]
المزيــد ...

ከአቡ ሙሐመድ ዐብደላህ ቢን ዐምር ቢን አልዓስ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
"አንዳችሁ ዝንባሌው ይዤ የመጣሁትን እስከሚከተል ድረስ አላመነም።"

-

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አንድ ሰው ውዴታው መልክተኛው -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይዘውት የመጡትን ትእዛዛትን፣ ክልከላዎችንና ሌሎችንም እስከሚከተል ድረስ፤ እርሳቸው ያዘዙትን እስኪወድና የከለከሉትንም እስኪጠላ ድረስ ኢማኑ የተሟላ አማኝ አይሆንም ብለው አብራሩ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ይህ ሐዲሥ ለሸሪዓ እጅ ለመስጠትና ታዛዥ ለመሆን መርህ የሆነ ሐዲሥ ነው።
  2. የአይምሮውን ወይም የባህሉን ፍርድ መልክተኛው -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይዘውት ከመጡት መመርያ የሚያስቀድም ሰው ከርሱ ላይ ኢማን ውድቅ መደረጉ ለሁሉም ሰው ማስጠንቀቂያ ነው።
  3. ሐዲሡ ላይ «ይዤው ለመጣሁት» ማለታቸው በሁሉም ነገር ሸሪዓን ማስዳኘት ግዴታ መሆኑን ያስረዳናል።
  4. ኢማን በአምልኮ ይጨምራል በወንጀል ደግሞ ይቀንሳል።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية الدرية الصربية الطاجيكية Kinjaruandisht المجرية التشيكية الموري الولوف Azerisht الأوزبكية الأوكرانية الجورجية المقدونية الخميرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ምድቦች
ተጨማሪ