+ -

عَن أَبِي أُمَامَةَ قَالَ: حَدَّثَنِي عَمْرُو بْنُ عَبَسَةَ رضي الله عنه أَنَّهُ سَمِعَ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«أَقْرَبُ مَا يَكُونُ الرَّبُّ مِنَ العَبْدِ فِي جَوْفِ اللَّيْلِ الآخِرِ، فَإِنْ اسْتَطَعْتَ أَنْ تَكُونَ مِمَّنْ يَذْكُرُ اللَّهَ فِي تِلْكَ السَّاعَةِ فَكُنْ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي] - [سنن الترمذي: 3579]
المزيــد ...

ከአቡ ኡማማ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «ዐምር ቢን ዐበሳህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ እንደሰማቸው ነገረኝ:
"ጌታ ወደ ባሪያ እጅግ ቅርብ የሚሆነው በመጨረሻው የሌሊቱ አጋማሽ ነው። በዚህ ወቅት አላህን ከሚያወሱ መሆን ከቻልክ ሁን!"»

[ሐሰን ነው።] - [ቲርሚዚ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 3579]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጥራት የተገባው ጌታ ወደ ባሪያ እጅግ ቅርብ የሚሆነው በመጨረሻው የሌሊቱ ሲሶ በመሆኑ አንተ አማኝ ሆይ! በዚህ ወቅት ከሚያመልኩት፣ ከሚሰግዱ፣ ከሚያወሱ፣ በወንጀላቸው ከሚፀፀቱ ሰዎች መካከል ለመሆን ከተሳካልህና ከቻልክ በዚህ ወቅት አጅር መሸመትና መታገል የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية النيبالية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አንድ ሙስሊም በሌሊቱ የመጨረሻ ወቅት ላይ ዚክር እንዲያደርግ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. በተለያዩ ወቅቶች ዚክር ለማለት፣ ዱዓ ለማድረግና ለመስገድ አንዱ አምልኮ ከአንዱ እንደሚበላለጥ እንረዳለን።
  3. "ጌታ ወደ ባሪያው እጅግ ቅርብ የሚሆነው" በሚለው ሐዲሥና "አንድ ባሪያ ወደ ጌታው እጅግ ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ላይ ሆኖ ነው።" በሚለው ሐዲሥ መካከል ባለው ልዩነት ሚረክ እንዲህ ብለዋል: እዛኛው ላይ የተፈለገው ጌታ ወደ ባሪያ እጅግ ቅርብ የሚሆነው የሌሊቱ አጋማሽ ላይ ሲሆን እዚህኛው ላይ የተፈለገው ደግሞ አንድ ባሪያ ካሉት ሁኔታዎች መካከል ወደ ጌታ የሚቀርበው በሱጁድ ሁኔታው መሆኑን ለመግለፅ ነው።