+ -

عَنْ صُهَيْبٍ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«إِذَا دَخَلَ أَهْلُ الْجَنَّةِ الْجَنَّةَ، قَالَ: يَقُولُ اللهُ تَبَارَكَ وَتَعَالَى: تُرِيدُونَ شَيْئًا أَزِيدُكُمْ؟ فَيَقُولُونَ: أَلَمْ تُبَيِّضْ وُجُوهَنَا؟ أَلَمْ تُدْخِلْنَا الْجَنَّةَ، وَتُنَجِّنَا مِنَ النَّارِ؟ قَالَ: فَيَكْشِفُ الْحِجَابَ، فَمَا أُعْطُوا شَيْئًا أَحَبَّ إِلَيْهِمْ مِنَ النَّظَرِ إِلَى رَبِّهِمْ عَزَّ وَجَلَّ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 181]
المزيــد ...

ከሱሀይብ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
«የጀነት ሰዎች ጀነት የገቡ ጊዜ አላህ ተባረከ ወተዓላ እንዲህ ይላል "አንዳች ነገር እንድጨምርላችሁ ትፈልጋላችሁን?" እነርሱም "ፊታችንን አላበራህልንምን? ጀነት አስገብተህስ ከእሳት አላዳንከንምን?" ይላሉ። ነቢዩ እንዲህ አሉ "የፊቱን ግርዶሽ ይገልጣል። ወደ ጌታቸው ዐዘ ወጀል ከመመልከት የበለጠ ተወዳጅ የሆነ አንዳችም ነገር አልተሰጣቸውም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 181]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የጀነት ሰዎች ጀነት የገቡ ጊዜ አላህ ተባረከ ወተዓላ ለነርሱ እንዲህ እንደሚል ተናገሩ:
እንድጨምርላችሁ የምትፈልጉት አንዳች ነገር አለን?
ሁሉም የጀነት ሰዎችም እንዲህ ይላሉ: ፊታችንን አላበራኸውምን? ጀነት አስገብተህስ ከእሳት አላዳንከንምን?
አላህም ግርዶሹን አስወግዶ ይገልጠዋል። የፊቱ ግርዶሽም ብርሃን ነው። ወደ ጌታቸው ዐዘ ወጀል ከመመልከት የበለጠ ተወዳጅ ነገርም አይሰጣቸውም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የጀነት ሰዎች ግርዶሹ ተገልጦ ጌታቸውን ሲመለከቱ ከሀዲያን ግን ጌታቸውን ከማየት የተነፈጉ ናቸው።
  2. ከጀነት ፀጋዎች ትልቁ ፀጋ አማኞች ጌታቸውን መመልከታቸው ነው።
  3. የጀነት ሰዎች ሁሉ ደረጃቸው የተለያየ ቢሆን እንኳ ጌታቸውን ይመለከታሉ።
  4. አላህ አማኞችን ጀነት በማስገባት ችሮታውን እንደሚውል እንረዳለን።
  5. በመልካም ተግባርና አላህንና መልክተኛውን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በመታዘዝ ወደ ጀነት መቻኮል አንገብጋቢ እንደሆነ እንረዳለን።