عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لاَ تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يَمُرَّ الرَّجُلُ بِقَبْرِ الرَّجُلِ فَيَقُولُ: يَا لَيْتَنِي مَكَانَهُ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
"አንድ ሰው በአንድ ሰው ቀብር በኩል እያለፈ 'ዋ ምኞቴ ምናለ በርሱ ስፍራ ላይ እኔ በነበርኩ!' እስኪል ድረስ ሰአቲቱ አትቆምም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ሰውዬው በቀብር በኩል እያለፈ ሞቶ በተቀበረው ፋንታ ሞቶ በነበር እስኪመኝ ድረስ ሰአቲቱ እንደማትቆም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ተናገሩ። የዚህ ምክንያትም ጥመትና የጥመት ባለቤቶች በመብዛታቸው፣ ፈተና፣ ወንጀልና ውግዝ ተግባራት ይፋ በመሆናቸው ሳቢያ ኢማኑ እንዳይጠፋ በነፍሱ ላይ በመፍራቱ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በመጨረሻው ዘመን ወንጀሎችና ፈተናዎች ይፋ እንደሚሆኑ መጠቆሙን እንረዳለን።
  2. ጥንቃቄ በማድረግ፣ በኢማንና በመልካም ስራ ለሞት መዘጋጀት እና ከፈተናና መከራ ስፍራዎች መራቅ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።