+ -

عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بنِ مَسْعُودٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: قَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لَيْسَ مِنَّا مَنْ لَطَمَ الخُدُودَ، وَشَقَّ الجُيُوبَ، وَدَعَا بِدَعْوَى الجَاهِلِيَّةِ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 1294]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"ጉንጩን የመታ፣ አንገትያውን የቀደደ፣ በድንቁርና ጥሪ የተጣራ ከኛ አይደለም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 1294]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከአንዳንድ የድንቁርና ዘመን ሰዎች ተግባር አስጠነቀቁም ከለከሉም። እንዲህም አሉ: እነዚህ ከኛ አይደሉም:
የመጀመሪያው: ጉንጩን የመታ ነው። ጉንጭን የለዩት በአብዛኛው የሚፈፀመው እርሱ ስለሆነ ነው እንጂ የተቀሩትን የፊት ክፍልን መምታትም ክልከላው ውስጥ ይካተታል።
ሁለተኛው: ልብስ ላይ ጭንቅላት እንዲገባበት ተብሎ የሚከፈተውን (አንገትያ) ከትእግስት ማጣት ብዛት መቅደድ ነው።
ሶስተኛው: የድንቁርና ዘመን ጥሪዎችን መጣራት ነው። ለምሳሌ ያህል፦ ወዮልኝ፣ ወይኔ በጠፋው ማለት፣ ሙሾ ማውረድ፣ እየገጠሙ ማለቃቀስና ሌሎችም ይጠቀሳሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሐዲሡ ውስጥ የመጣው ይህ (ከእኛ አይደሉም የሚለው) ዛቻ እነዚህ ተግባራት ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል መሆናቸውን ይጠቁማል።
  2. በመከራ ላይ መታገስ ግዴታ መሆኑንና አሳማሚ በሆኑ የአላህ ውሳኔዎች ላይ መበሳጨት ክልክል መሆኑን እንረዳለን። የዚህም መገለጫው: ሙሾ በማውረድ ወይም እየገጣጠሙ በማልቀስ ወይም በመላጨት ወይም በመቀዳደድ ወይም ከዚህም ውጪ ያለን በመስራት ነው።
  3. ሸሪዓ ያላፀደቀውን የድንቁርና ዘመን ጉዳዮችን መከተል ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  4. ማዘንና ማልቀስ በአላህ ውሳኔ ላይ ከመታገስ ጋር ስለማይፃረር ችግር የለውም። ማልቀስ አላህ በቅርብ ዘመዶችና ወዳጆች ቀልብ ውስጥ ያደረጋት እዝነት ናት።
  5. ሙስሊም የሆነ ሰው በአላህ ፍርድ መውደድ አለበት። ባይወድ እንኳን መታገስ ግዴታው ነው።
ተጨማሪ