عَنْ جَرِيرِِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ رضي الله عنه قَالَ:
بَايَعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَلَى شَهَادَةِ أَنْ لاَ إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ، وَإِقَامِ الصَّلاَةِ، وَإِيتَاءِ الزَّكَاةِ، وَالسَّمْعِ وَالطَّاعَةِ، وَالنُّصْحِ لِكُلِّ مُسْلِمٍ.

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከጀሪር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦
"የአላህን መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን በመመስከር፣ ሶላትን በማቋቋም፣ ዘካን በመስጠት፣ መሪዎችን በመስማትና በመታዘዝ ላይ፣ ለሁሉም ሙስሊም ተቆርቋሪ (ታማኝ/ ቅን) በመሆን ላይ ቃል ኪዳን ተጋቧሃቸው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ሶሐቢዩ ጀሪር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ዘንድ እንደነበርና እርሳቸውንም ቃልኪዳን እንደተጋባ ተናገረ። ቃል የተጋባውም በተውሒድ (አላህን በብቸኝነት በማምለክ)፣ በቀንና ምሽት አምስት ግዴታ የሆኑትን ሶላቶች ‐ መስፈርቶቿን፣ ማእዘናቶቿን፣ ግዴታዎቿንና ሱናዎቿን በማሟላት ‐ በመስገድ፣ ግዴታ የሆነውን ዘካ በመስጠት ላይ ‐ ዘካ: ግዴታ የሆነ ገንዘባዊ አምልኮ ሲሆን ከሀብታሞች ተወስዶ ለሚገባቸው ድሆችና ለሌሎችም የሚሰጥ ነው፣ ‐ መሪዎችን በመታዘዝ ላይ፣ ለሁሉም ሙስሊም ተቆርቋሪ (ቅን) በመሆን ላይ ‐ ይህም: ለሙስሊም ጥቅም በመጓጓት፣ መልካምን ለርሱ በማድረስ፣ በንግግርም ሆነ በተግባር መጥፎን ነገር ከርሱ በመከላከል ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የሶላትና የዘካን አንገብጋቢነት እንረዳለን። እነርሱም የኢስላም ማእዘናት ናቸው።
  2. የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከሶሐቦች (ረዲየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና ጋር በዚህ ጉዳይ ቃል ኪዳን መጋባታቸው በሙስሊሞች መካከል የታማኝነትና የመመካከርን አንገብጋቢነት ያስረዳል።
ተጨማሪ