عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«أَمَا يَخْشَى أَحَدُكُمْ - أَوْ: لاَ يَخْشَى أَحَدُكُمْ - إِذَا رَفَعَ رَأْسَهُ قَبْلَ الإِمَامِ، أَنْ يَجْعَلَ اللَّهُ رَأْسَهُ رَأْسَ حِمَارٍ، أَوْ يَجْعَلَ اللَّهُ صُورَتَهُ صُورَةَ حِمَارٍ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
"አንዳችሁ ከኢማም በፊት ጭንቅላቱን ቀና ያደረገ ጊዜ አላህ ጭንቅላቱን የአህያ ጭንቅላት እንዳያደርገው ወይም አላህ የሰውነት ቅርፁን የአህያ የሰውነት ቅርፅ እንዳያደርግበት አይፈራምን?!"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጭንቅላቱን ከኢማሙ በፊት ቀና የሚያደርግ ሰው አላህ ጭንቅላቱን የአህያ ጭንቅላት ሊያደርግበት ወይም የሰውነት ቅርፁን የአህያ ቅርፅ ሊያደርግበት እንደሚችል በመግለፅ ከባድ ዛቻን አስተላለፉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አንድ ተከታይ ከኢማሙ ጋር ያለው የመከተል ሁኔታ አራት ነው። ከአራቱ ሶስቱ የተከለከሉ ናቸው። እነርሱም: መቅደም፣ እኩል መፈፀምና ኋላ መቅረት ናቸው። ለተከታይ የተደነገገው ኢማሙን መከተል ነው።
  2. ተከታይ የሆነ ሰው ሶላት ውስጥ ኢማሙን መከተል ግዴታው እንደሆነ እንረዳለን።
  3. ከኢማሙ በፊት ራሱን ቀና የሚያደርግ ሰው ላይ የሰውነት ቅርፁ ወደ አህያ ቅርፅ እንደሚለወጥ የመጣው ዛቻ ሊሆን የሚችል ነገር ነው። ይህም ወደ ሌላ ፍጥረት ከመለወጥ የሚመደብ ነው።