+ -

عَنْ وَابِصَةَ رضي الله عنه:
أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ رَأَى رَجُلًا صَلَّى وَحْدَهُ خَلْفَ الصَّفِّ، فَأَمَرَهُ أَنْ يُعِيدَ صَلَاتَهُ.

[حسن] - [رواه أبو داود والترمذي وابن ماجه وأحمد] - [مسند أحمد: 18000]
المزيــد ...

ከዋቢሰህ (ረዺየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:
"የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አንድ ሰውዬ ከሰልፍ ኋላ ብቻውን ሲሰግድ ተመለከቱትና ሶላቱን እንዲደግመው አዘዙት።"

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ፣ ቲርሚዚ፣ ኢብኑማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሙስነድ አሕመድ - 18000]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አንድ ሰውዬ ለብቻው ከሰልፍ ኋላ ተመለከቱትና ሶላቱን በዚህ ሁኔታ መሰገዱ ትክክለኛነቷን ስለሚያጠፋ ሶላቱን እንዲደግመው አዘዙት።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የህብረት ሶላት ለመስገድ በጊዜ መስጂድ በመግባትና ወደፊት ቀደም በማለት መነሳሳቱን እንረዳለን። ሶላቱ ለመበላሸት እንዳትጋለጥም ከሰልፍ ኋላ ለብቻው አለመስገድንም ያነሳሳል።
  2. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ሶላትን ከሰልፍ ኋላ ለብቻው ከጀመረ በኃላ ከሩኩዕ ከመነሳቱ በፊት ወደ ሰልፍ የገባ ሰው በአቢ በክራህ ሐዲሥ ውስጥ እንደመጣው የመድገም ግዴታ የለበትም። ያለበለዚያ ግን የዋቢሰህ ሐዲሥ ጥቅል ሀሳብ እንደሚያስረዳን የመድገም ግዴታ ይጠበቅበት ነበር።»