عَنْ عَبْدِ اللهِ بنِ مَسْعُودٍ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«أَوَّلُ مَا يُقْضَى بَيْنَ النَّاسِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ فِي الدِّمَاءِ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 1678]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
«የትንሳኤ ቀን በሰዎች መካከል መጀመሪያ የሚፈረደው ጉዳይ የደም ጉዳይ ነው።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1678]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የትንሳኤ ቀን በሰዎች መካከል መጀመሪያ የሚፈረደው ጉዳይ ከፊሉ ከፊሉን የሚበድልበት በሆነው እንደመግደልና ማቁሰል ያሉ የደም ጉዳዮች መሆኑን አወሱ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የደም ጉዳይ ከባድ መሆኑን እንረዳለን። ፍርድ የሚጀመረው በአንገብጋቢው ጉዳይ ነውና።
  2. ወንጀሎች የሚተልቁት በርሱ ምክንያት የሚከሰቱ ብክለቶች እንደመተለቃቸው መጠን ነው። ንፁህ ነፍስን ማጥፋት ደግሞ ከትላልቅ ብክለቶች መካከል አንዱ ነው። በአላህ ማጋራትና ኩፍር (ክህደት) እንጂ ምንም ከርሱ የሚከፋ ወንጀልም የለም።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (55)