عَنْ أَبِي ثَعْلَبَةَ الخُشَنِيِّ جُرْثُومِ بن نَاشِرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَال:
«إِنَّ اللَّهَ فَرَضَ فَرَائِضَ فَلَا تُضَيِّعُوهَا، وَحَدَّ حُدُودًا فَلَا تَعْتَدُوهَا، وَحَرَّمَ أَشْيَاءَ فَلَا تَنْتَهِكُوهَا، وَسَكَتَ عَنْ أَشْيَاءَ رَحْمَةً لَكُمْ غَيْرَ نِسْيَانٍ فَلَا تَبْحَثُوا عَنْهَا».
[قال النووي: حديث حسن] - [رواه الدارقطني في سننه، وغيره] - [الأربعون النووية: 30]
المزيــد ...
ከአቡ ሠዕለባ አልኹሸኒይ ጁርሡም ቢን ናሺር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል:
"አላህ ግዴታዎችን ደነግጓል። (ባለመስራት) አታጥፏት። ድንበሮችን ወስኗል። አትተላለፏት። ነገሮችን ከልክሏል አትዳፈሯት። ለናንተው በማዘን ሳይረሳው አንዳንድ ነገሮችንም ዝም ብሏል፤ ስለርሷ አትፈላፈሉ።"
[قال النووي: حديث حسن] - [رواه الدارقطني في سننه وغيره] - [الأربعون النووية - 30]
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ በማለት ተናገሩ። አላህ ብዙ ነገሮችን ግዴታ አድርጓልም ደንግጓልም። አጥብቃችሁ ያዙት፤ በመተው ወይም በመዘናጋት እንዳታጓድሉት። አላህ እናንተን የሚያቅቡና እርሱ ከማይወደው የሚያግዷችሁን የተወሰኑ ማቀቢያዎችንና ማገጃዎችን አድርጓልና በሸሪዓ ካዘዘው አትለፉ። አላህ ውግዝ ነገሮችን ስለከለከለ አትፈፅሟትም አትቅረቧትም። ከነዚህ ውጪ ያሉን ግን ለባሮቹ በማዘን ትቷቸዋል ዝምም ብሏቸዋል። ልክ በመሰረቱ እንደነበረው ፍቁድ እንደሆነ ይቀራል። ስለርሱም አትፈላፈሉ።