+ -

عَنْ عَبْدِ اللهِ بْنِ مُغَفَّلٍ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم:
«بَيْنَ كُلِّ أَذَانَيْنِ صَلَاةٌ، بَيْنَ كُلِّ أَذَانَيْنِ صَلَاةٌ» ثُمَّ قَالَ فِي الثَّالِثَةِ: «لِمَنْ شَاءَ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 627]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን ሙገፈል (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ «ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦
"በየሁሉም ሁለት አዛኖች መካከል ሶላት አለ። በየሁሉም ሁለት አዛኖች መካከል ሶላት አለ።" ቀጥለው በሶስተኛው "ለፈለገ ሰው" አሉ።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 627]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በየሁሉም አዛንና ኢቃም መካከል ሱና ሶላት እንዳለ ገለፁ። ይህንንም ሶስት ጊዜ ደጋገሙት። በሶስተኛውም ይህን ሶላት መስገድ ለፈለገ ሰው ተወዳጅ እንደሚሆንለት ተናገሩ።

ትርጉም: የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ታጋሎግ ሃውሳ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በአዛንና ኢቃም መካከል ሶላት መስገድ ተወዳጅ መሆኑን እንረዳለን።
  2. ንግግርን መደጋገም የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና መመሪያ እንደሆነ እንረዳለን። ይህም የሚናገሩት ነገር አንገብጋቢ መሆኑን አፅንዖት ለመስጠትና ለማሰማት ብለው ነው።
  3. በሁለት አዛን በማለት የተፈለገው: አዛንና ኢቃምን ነው። (ሁለቱ አዛኖች) ያሉት ወደ አንዱ በማመዘን ነው። (ፀሃይና ጨረቀን) ሁለቱ ጨረቃዎች እንደሚባሉት፣ (አቡበከርና ዑመር) ሁለቱ ዑመሮች እንደሚባሉት ማለት ነው።
  4. አዛን ማለት ወቅት መግባቱን ማሳወቂያ ነው። ኢቃማህ ማለት ደግሞ ሶላት መፈፀሚያ ወቅቱ መድረሱን ማሳወቂያ ነው።
ተጨማሪ