+ -

عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ رضي الله عنهما أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«مَنْ قَالَ حِينَ يَسْمَعُ النِّدَاءَ: اللَّهُمَّ رَبَّ هَذِهِ الدَّعْوَةِ التَّامَّةِ، وَالصَّلاَةِ القَائِمَةِ، آتِ مُحَمَّدًا الوَسِيلَةَ وَالفَضِيلَةَ، وَابْعَثْهُ مَقَامًا مَحْمُودًا الَّذِي وَعَدْتَهُ، حَلَّتْ لَهُ شَفَاعَتِي يَوْمَ القِيَامَةِ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 614]
المزيــد ...

ከጃቢር ቢን ዐብዲላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"አዛን በሚሰማ ጊዜ ‹አልላሁመ ረበ ሀዚሂ አድደዕወቲ አትታመቲ ወስሰላቲል ቃኢመህ አቲ ሙሐመደኒል ወሲለተ ወልፈዲለተ ወብዐሥሁ መቃመን መሕሙደኒለዚ ወዐድተህ› ያለ ሰው የትንሳኤ ቀን ምልጃዬ ትፀድቅለታለች።" ትርጉሙም "የዚህ የተሟላ ጥሪና የምትቆመው ሶላት ጌታ የሆንከው አላህ ሆይ! ለሙሐመድ ወሲላና ፈዲላን ስጣቸው፤ ቃል የገባህላቸውን ምስጉን ስፍራም ስጣቸው።" ማለት ነው።

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 614]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አዛን ባይን በሚሰማ ጊዜ አዛኑን ካጠናቀቀ በኋላ እንዲህ የሚል ሰውን ገለፁ።
(የዚህ የተሟላ ጥሪ ጌታ የሆንከው አላህ ሆይ!) የተሟላ ጥሪ የተባለው ወደ አላህ አምልኮና ወደ ሶላት የሚጠራበት የሆነው የአዛን ጥሪ ነው። (የተሟላ) ማለት መልዕክቱና የተውሒድ ጥሪው የተሟላ የሆነው ማለት ነው። (የቆመችው ሶላትም ጌታ) ማለት ዘውታሪ የሆነችው ሶላት ማለት ነው። (ለሙሐመድ ወሲላን ስጥ) ማለት ለነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ካልሆነ በቀር ለማንም የማትገባ የሆነችው ጀነት ውስጥ ያለች ከፍተኛዋን ደረጃ ስጣቸው፤ (ፈዲላንም) ማለት ከፍጡራን ደረጃዎች በላይ ከፍ ያለች ደረጃንም ስጣቸው። (ምስጉኑን ስፍራም ስጣቸው) ማለት እዛ ቦታ የቆመ ምስጉን የሚሆንበት ስፍራ ነው። እርሱም የትንሳኤ ቀን ያለው ትልቁ ምልጃ ነው። (ቃል የገባህላቸው የሆነውን) ማለት {ጌታህ ምስጉን በሆነ ስፍራ በእርግጥ ያቆምሃል።} በሚለው ቃልህ ለነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንድትሆን ቃል የገባኸውን ስፍራ ስጣቸው ማለት ነው።
ይህን ዱዓ የለመነም ሰው የትንሳኤ ቀን የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምልጃ ይረጋገጥለታልም ይፀድቅለታልም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ይህን ዱዓ ከሙአዚን ኋላ የሚለውን ከደጋገሙ በኋላ ሲያጠናቅቅ ማለቱ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን። አዛን ያልሰማ ሰው ግን ይህን ዱዓ አይልም።
  2. ወሲላን፣ ፈዲላን፣ ምስጉን ስፍራንና በፍጡራን መካከል ፍርድ እንዲካሄድ ትልቁን ምልጃ ለነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና መሰጠቱ የርሳቸውን ደረጃ ያሳየናል።
  3. "የትንሳኤ ቀን ምልጃዬ ትፀድቅለታለች።" ከሚለው ንግግራቸው መልክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንደሚያማልዱ እናፀድቃለን።
  4. የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምልጃ ከኡመታቸው ትላልቅ ወንጀል ለሰሩት እሳት እንዳይገቡ እና እሳት ለገቡት ደግሞ እንዲወጡ ማማለድ ነው። ወይም ወደ ጀነት ያለሒሳብ እንዲገቡ ማማለድ እና ጀነት የገቡትም ደረጃቸው ከፍ እንዲል ማማለድ ነው።
  5. ጢቢይ እንዲህ ብለዋል: «የተሟላች ጥሪ የተባለችው ከመጀመሪያው የአዛን ክፍል "ሙሐመደን ረሱሉሏህ" እስከሚለው ድረስ ያለው ነው። ሶላትን የሚያቋቁሙ በሚለው ውስጥ የቆመች የተባለችው ሶላት ደግሞ "ሐየዐለህ" ናት። ሶላት በማለት የተፈለገው ዱዓ፤ የቆመችው በማለት የተፈለገው ደግሞ ዘውታሪ ሊሆንም ያስመቻል። በአንድ ነገር የዘወተረ ጊዜ ቆመ እንደሚባለው ማለት ነው። በዚህም መሰረት "የቆመችው ሶላት" የሚለው የተሟላች ጥሪ ለሚለው መግለጫ ነው። ሶላት በማለት የተፈለገው አሁን አዛን እየተጠራላት ያለችው ሶላት ለማለት ተፈልጎ ሊሆንም ይችላል። ቃሉ በግልፅ የሚያስረዳውም ይህንኑ ነው።»
  6. ሙሀለብ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ በሶላት ወቅቶች ዱዓ ማድረግ ላይ ያነሳሳል። በአዛን ወቅት ዱዓ ማድረግ ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ ተስፋ የሚደረግበት ወቅት ነውና።"