+ -

عَنْ عُقْبَةَ بْنِ عَامِرٍ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ: قَالَ لِي رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«أُنْزِلَ -أَوْ أُنْزِلَتْ- عَلَيَّ آيَاتٌ لَمْ يُرَ مِثْلُهُنَّ قَطُّ، الْمُعَوِّذَتَيْنِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 814]
المزيــد ...

ከዑቅበህ ቢን ዓሚር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ አሉኝ:
"እንደነርሱ አምሳያ በጭራሽ ያልታየ አንቀጾች በኔ ላይ ወርዷል ወይም ወርደውልኛል። እነርሱም 'ሙዐወዘተይን' ናቸው።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 814]

ትንታኔ

ዑቅባ ቢን ዓሚር (ረዺየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለርሱ እንዲህ እንዳሉት ተናገረ: (ጥበቃን በመፈለግ በኩል) እንደነርሱ አምሳያ በጭራሽ ያልታየን አንቀጾች ዛሬ ምሽት አላህ በኔ ላይ አወረደ። እነርሱም ሙዐወዘተይን ናቸው። የ{ፈለቅ} ምዕራፍና የ{አንናስ} ምዕራፍ ናቸው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የእነዚህ ሁለት ምዕራፍ ደረጃ ትልቅነት መገለፁን እንረዳለን።
  2. በሁለቱ ምዕራፎች ከሁሉም ክፋቶች ጥበቃን በመፈለግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الموري Malagasisht الولوف الأوكرانية الجورجية المقدونية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ተጨማሪ