+ -

عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الخُدْرِيِّ رَضيَ اللهُ عنهُ:
أَنَّ رَجُلًا سَمِعَ رَجُلًا يَقْرَأُ: {قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ} يُرَدِّدُهَا، فَلَمَّا أَصْبَحَ جَاءَ إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَذَكَرَ ذَلِكَ لَهُ، وَكَأَنَّ الرَّجُلَ يَتَقَالُّهَا، فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ إِنَّهَا لَتَعْدِلُ ثُلُثَ القُرْآنِ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 5013]
المزيــد ...

ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:
«አንድ ሰውዬ የሆነ ሰው {ቁል ሁወሏሁ አሐድ}ን እየደጋገመ ሲያነብ ሰማ። የነጋም ጊዜ ወደ አላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በመምጣት ነገሩን በሚያቃልል ሁኔታ ይህንን አወሳላቸው። የአላህም መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- "ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! እርሷ (ቁል ሁወሏሁ አሐድ) የቁርአንን ሲሶ ትስተካከላለች።" አሉ።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 5013]

ትንታኔ

አቡ ሰዒድ አልኹድሪይ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዳወሱት: አንድ ሰውዬ ሌላ ሰው የ{ቁል ሁወሏሁ አሐድ}ን ምዕራፍ ሲያነብ ሰማ። ምሽቱን ሁሉ ሌላ ምዕራፍ ሳይጨምር እርሷን ብቻ ነበር እየደጋገመ የሚያነበው። የነጋም ጊዜ ወደ አላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በመምጣት ይህንን አወሳላቸው። የጠያቂው አነጋገርም ምዕራፏን ያሳነሳት ይመስላል። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አፅንዖት ለመስጠት በመማል "ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! እርሷ የቁርአንን ሲሶ ትስተካከላለች።" አሉ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የኢኽላስ ምዕራፍ ትሩፋትን እንረዳለን። እርሷም የቁርአንን ሲሶ የምትስተካከል መሆኗ፤
  2. የለይል ሶላት ሲሰገድ ጥቂት አንቀጾችን በመቅራትና እነርሱን በመደጋገም መስገድ እንደሚፈቀድ፤ ይህንንም አሳንሶ ማየት እንደማይገባ እንረዳለን።
  3. ማዚሪይ እንዲህ ብለዋል: «በሐዲሡ ለማለት የተፈለገውን በማስመልከት "ቁርአን ሶስት ክፍሎች አሉት። እነርሱም: ታሪክ፣ ህግጋትና የአላህ ባህሪያት ናቸው። {ቁል ሁወሏሁ አሐድ} የአላህን ባህሪ ብቻ የምታወሳ ናት። ስለዚህ ከሶስቱ ክፍሎች አንዱ ክፍል ናት ማለት ነው።" ተብሏል። ይህቺን ምዕራፍ ማንበብ የሚያስገኘው ምንዳ ሲነባበር የቁርአን ሲሶ ሲነበብ ሳይነባበር የሚያስገኘውን ያህል ይሆናል ማለት ነውም ተብሏል።»
ትርጉም: እንግሊዝኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ተጨማሪ