عن أبي هريرة رضي الله عنه: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:
«قَالَ اللهُ تَعَالَى: قَسَمْتُ الصَّلَاةَ بَيْنِي وَبَيْنَ عَبْدِي نِصْفَيْنِ، وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ، فَإِذَا قَالَ الْعَبْدُ: {الْحَمْدُ لِلهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ}، قَالَ اللهُ تَعَالَى: حَمِدَنِي عَبْدِي، وَإِذَا قَالَ: {الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ}، قَالَ اللهُ تَعَالَى: أَثْنَى عَلَيَّ عَبْدِي، وَإِذَا قَالَ: {مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ}، قَالَ: مَجَّدَنِي عَبْدِي، -وَقَالَ مَرَّةً: فَوَّضَ إِلَيَّ عَبْدِي-، فَإِذَا قَالَ: {إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ}، قَالَ: هَذَا بَيْنِي وَبَيْنَ عَبْدِي وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ، فَإِذَا قَالَ: {اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ، صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلا الضَّالِّينَ}، قَالَ: هَذَا لِعَبْدِي وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ ብለዋል፦
"ከፍ ያለው አላህ እንዲህ አለ: 'ሶላትን በኔና በባሪያዬ መካከል ለሁለት ከፈልኩት። ለባሪያዬም የጠየቀው አለው። ባሪያዬ {الْحَمْدُ لِلهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ} (ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው፤ የዓለማት ጌታ ለሆነው።) ያለ ጊዜ አላህ 'ባሪያዬ አመሰገነኝ!' ይላል። ባሪያው {الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ} (እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ ለሆነው።) ያለ ጊዜ አላህ 'ባሪያዬ እኔን አወደሰ!' ይላል። ባሪያው {مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ} (የፍርዱ ቀን ባለቤት ለሆነው።) ያለ ጊዜ አላህም 'ባሪያዬ አላቀኝ!' ይላል። - እንዲሁም 'ባርያዬ ጉዳዩን ወደ እኔ አስጠጋ።' - ይላል። ባሪያው {إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ} (አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታ እንለምናለን።) ያለ ጊዜ አላህም 'ይህ በኔና በባሪያዬ መካከል ያለ ቃል ኪዳን ነው። ለባሪያዬም የጠየቀውን አለው።' ይላል። ባሪያው {اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ، صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلا الضَّالِّينَ} (ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፤ የእነዚያን በነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ (ምራን በሉ።) ) ያለ ጊዜ አላህም 'ይህ ለባሪያዬ ነው። ለባሪያዬም የጠየቀው አለው።' ይላል።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከፍ ያለው አላህ በሐዲሠል ቁድስ እንዲህ እንዳለ ተናገሩ። "የፋቲሐን ምእራፍ በሶላት ውስጥ በኔና በባሪያዬ መካከል ለሁለት ከፈልኩት። ግማሹ ለኔ ግማሹ ለርሱ ነው።
የመጀመሪያው ክፍል: ለአላህ ምስጋና፣ ውዳሴና ልቅና ማቅረብ ሲሆን በዚህ ላይ ምርጥ ምንዳን እመነዳዋለሁ።
ሁለተኛው ክፍል: መዋደቅ፣ ዱዓ ማድረግ ሲሆን እቀበለዋለሁም የጠየቀኝንም እሰጠዋለሁ።
ሰጋጁ {الْحَمْدُ لِلهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ} (ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው፤ የዓለማት ጌታ ለሆነው።) ያለ ጊዜ አላህ "ባሪያዬ አመሰገነኝ!" ይላል። ሰጋጁ {الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ} (እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ ለሆነው።) ያለ ጊዜ አላህም "ባሪያዬ በኔ ላይ አወደሰ፣ አሞገሰኝም፣ በፍጡሮቼ ላይ አጠቃላይ ፀጋዎችን መዋሌንም እውቅናን ሰጠ።" ይላል። ሰጋጁ {مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ} (የፍርዱ ቀን ባለቤት ለሆነው።) ያለ ጊዜ አላህም "ባሪያዬ አላቀኝ!" ይላል። ይህም ትልቅ ክብር ነው።
ሰጋጁ {إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ} (አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታ እንለምናለን።) ያለ ጊዜ አላህም: "ይህ በኔና በባሪያዬ መካከል ያለ ቃል ኪዳን ነው። ይላል።
የዚህ አንቀፅ የመጀመሪያው ግማሽ ለአላህ ነው። እሱም (አንተን ብቻ እንግገዛለን።) የሚለው ነው። ይህም በአላህ ተመላኪነት እውቅና መስጠትና በዒባዳ ምላሽ መስጠት ነው። በዚህም በአንቀፁ ውስጥ ለአላህ የሆነው የመጀመሪያው ግማሽ ይጠናቀቃል።
የአንቀፁ ሁለተኛው ግማሽ ደግሞ ለባሪያው ነው። እሱም (አንተንም ብቻ እርዳታ እንለምናለን።) የሚለው ነው። ይህም ከአላህ እገዛ መፈለግና አላህ ባሮቹን ለማገዝ የገባውን ቃልኪዳኑን መከጀል ነው።
ሰጋጁ {اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ، صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلا الضَّالِّينَ} (ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፤ የእነዚያን በነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ (ምራን በሉ።) ) ያለ ጊዜ አላህም "ይህ ከባሪያዬ የመጣ መዋደቅና ተማፅኖ ነው። ለባሪያዬም የጠየቀው አለው። ልመናውን ተቀብዬዋለሁ።" ይላል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የፋቲሐን ታላቅነት እንረዳለን። የላቀው አላህ "ሶላት" ብሎ ጠርቷታል።
  2. ባሪያው አላህን በማመስገኑ፣ በማወደሱና በማላቁ ብቻ አላህም ባሪያውን ማወደሱ የጠየቀውንም እንደሚሰጠው ቃል መግባቱ አላህ ለባሪያው የሰጠውን ትኩረት ግልፅ ያደርግልናል።
  3. ይህቺ የተከበረች ምእራፍ አላህን ማመስገንን፣ የመመለሻውን ዓለም ማስታውስን፣ አላህን መለመንን፣ አምልኮን ለአላህ ማጥራትን፣ ወደ ቀጥተኛው መንገድ መመራትን መጠየቅን፣ ከጥመት መንገዶች ማስጠንቀቅን ሰብስባለች።
  4. አንድ ሰጋጅ ፋቲሐን በሚቀራ ጊዜ ይህንኑ ሐዲሥ ማስተዋሉ ሶላቱ ውስጥ የሚኖረውን ተመስጦ ይጨምርለታል።