عَنْ يحيى بنِ عُمَارةَ المَازِنِيِّ قَالَ:
شَهِدْتُ عَمْرَو بْنَ أَبِي حَسَنٍ سَأَلَ عَبْدَ اللَّهِ بْنَ زَيْدٍ، عَنْ وُضُوءِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَدَعَا بِتَوْرٍ مِنْ مَاءٍ، فَتَوَضَّأَ لَهُمْ وُضُوءَ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَأَكْفَأَ عَلَى يَدِهِ مِنَ التَّوْرِ، فَغَسَلَ يَدَيْهِ ثَلاَثًا، ثُمَّ أَدْخَلَ يَدَهُ فِي التَّوْرِ، فَمَضْمَضَ وَاسْتَنْشَقَ وَاسْتَنْثَرَ، ثَلاَثَ غَرَفَاتٍ، ثُمَّ أَدْخَلَ يَدَهُ فَغَسَلَ وَجْهَهُ ثَلاَثًا، ثُمَّ غَسَلَ يَدَيْهِ مَرَّتَيْنِ إِلَى المِرْفَقَيْنِ، ثُمَّ أَدْخَلَ يَدَهُ فَمَسَحَ رَأْسَهُ، فَأَقْبَلَ بِهِمَا وَأَدْبَرَ مَرَّةً وَاحِدَةً، ثُمَّ غَسَلَ رِجْلَيْهِ إِلَى الكَعْبَيْنِ.

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከየሕያ ቢን ዑማረህ አልማዚኒይ እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
"ዐምር ቢን አቢ ሐሰን ለዐብደላህ ቢን ዘይድ ስለ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የዉዱእ አደራረግ ሲጠይቁ ተገኝቼ ነበር። ውሃ የያዘ እቃ እንዲመጣላቸው ጠየቁ። የነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዉዱእ አደራረግ አደረጉላቸው። ከዉዱእ እቃው ውሃን ወደ እጃቸው በማፍሰስ ሶስት ጊዜ እጃቸውን አጠቡ። ቀጥሎ እጃቸውን ወደ እቃው በመክተት ሶስት ጊዜ ውሃ እየዘገኑ ተጉመጠመጡ፤ አፍንጫቸው ውስጥ ውሃ በመክተትም አወጡ። ቀጥሎ እጃቸውን በመክተት ሶስት ጊዜ ፊታቸውን ታጠቡ። ቀጥሎ ሁለት ጊዜ ሁለት እጃቸውን እስከ ክርኖቻቸው አጠቡ። ቀጥሎ እጃቸውን በመክተት ጭንቅላታቸውን አበሱ። እጃቸውን አንድ ጊዜ ወደኋላ ወስደው ወደፊት መለሷቸው። ቀጥሎ ሁለት እግሮቻቸውን እስከ ቁርጭምጭሚታቸው ድረስ አጠቡ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ዐብደላህ ቢን ዘይድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና ስለ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዉዱእ አደራረግ በተግባራዊ መልኩ ገለፁ። አነስ ያለ ውሃ የያዘ እቃ እንዲያመጣላቸው ጠየቁ። በመጀመሪያ ሁለት መዳፋቸውን በማጠብ ጀመሩ። እቃውን ዘንበል በማድረግ ውሃውን እያፈሰሱ ሁለት እጆቻቸውን ከእቃው ውጪ አድርገው ሶስት ጊዜ አጠቧቸው። ቀጥለውም እጃቸውን እቃ ውስጥ በመክተት ከርሱ ሶስት ጊዜ እየዘገኑ በያንዳንዱ መዝገን ተጉመጠመጡ አፍንጫቸውም ውስጥ ውሃ እየከተቱ አስወጡ። ቀጥሎ ከእቃው በመዝገን ሶስት ጊዜ ፊታቸውን አጠቡ። ቀጥሎ ከእቃው በመዝገን ሁለት እጃቸውን እስከ ክርናቸው ድረስ ሁለት ጊዜ አጠቡ። ቀጥሎ ሁለት እጃቸውን እቃ ውስጥ በመክተት ካረጠቡ በኋላ ጭንቅላታቸውን በሁለት እጆቻቸው አበሱ። ከጭንቅላታቸው ፊትለፊት በመጀመር ወደ ማጅራታቸው እስኪደርስ ድረስ አበሱ። ቀጥሎ ወደ ጀመሩበት ስፍራ እስኪደርስ ድረስ ሁለት እጃቸውን መለሷቸው። ቀጥሎ ሁለት እግሮቻቸውን ከቁርጭምጭሚታቸው ጋር አጠቡ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አስተማሪ የሆነ ሰው እውቀቱ እንዲሰርፅና እንዲገነዘቡት እጅግ ቅርብ የሆነን መንገድ መጠቀም እንዳለበት እንረዳለን። ከነዚህም ውስጥ በተግባር ማስተማር አንዱ ነው።
  2. ከዉዱእ አካላት መካከል አንዳንዱን ሶስት ጊዜ መደጋገምና አንዳንዱንም ሁለት ጊዜ መድገም እንደሚፈቀድ እንረዳለን። ግዴታው ግን አንድ ጊዜ ማጠብ ነው።
  3. ሐዲሡ ላይ በመጣው መልኩ በዉዱእ አካላት መካከል ቅደም ተከተልን መጠበቅ ግዴታ ነው።
  4. የፊት ክልል በርዝማኔ ከተለምዶው የጭንቅላት ፀጉር መብቀያ ፂም እስከወረደበትና እስከ አገጭ ሲሆን በአግድም ደግሞ ከጆሮ እስከ ጆሮ ነው።