+ -

عن عائشةَ أمِّ المؤْمنِين رضي الله عنها قالت:
لَمْ يَكُنِ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَلَى شَيْءٍ مِنَ النَّوَافِلِ أَشَدَّ مِنْهُ تَعَاهُدًا عَلَى رَكْعَتَيِ الفَجْرِ.

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 1169]
المزيــد ...

ከአማኞች እናት ዓኢሻ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች:
"ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የፈጅር ሁለቱ ረከዓን (ቀብሊያ) ለመስገድ የሚያደርጉትን አይነት መጠባበቅ ለሌላ ሱና ሶላት አድርገው አይጠባበቁም ነበር።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 1169]

ትንታኔ

የአማኞች እናት ዓኢሻ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንዲህ ብላ ተናገረች: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የፈጅር ሁለቱ ረከዓን (ቀብሊያ) እጅግ ተጠባብቀውና ዘውትረው እንደሚሰግዱት ያህል ምንም ሱና ሶላት ተጠባብቀውና ዘውትረው አይሰግዱም ነበር።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነዋፊል (ተጨማሪ) ሶላቶች የሚባሉት: ከግዴታ ሶላቶች ውጪ ያሉ ማለት ነው። እዚህ ሐዲሥ ላይ የተፈለገውም ከግዴታ ሶላቶች በፊትና በኋላ ተከትለው የሚሰገዱ ሶላቶች ማለት ነው።
  2. ሱነን አርረዋቲብ የሚባሉት: ከፈጅር በፊት ሁለት ረከዓ፣ ከዝሁር በፊት አራት ረከዓ ከዝሁር በኋላ ሁለት ረከዓ፣ ከመግሪብ በኋላ ሁለት ረከዓ፣ ከዒሻ በኋላ ሁለት ረከዓ ናቸው።
  3. የፈጅር ቀብሊያ በመኖርያ ሀገር ላይም ሆነ ጉዞ ላይ ይሰገዳል። የዝሁር፣ የመግሪብና የዒሻ ቀብሊያና ባዕዲያ ሶላቶች ግን በመኖርያ ሀገር ላይ ብቻ ነው የሚሰገዱት።
  4. የፈጅር ሁለቱ ረከዓ ቀብሊያ አፅንዖት የተሰጠው ተወዳጅ ሶላት ስለሆነ ችላ ሊባል አይገባውም።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ