عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رضي الله عنهما قَالَ:
مَرَّ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ بِقَبْرَيْنِ، فَقَالَ: «إِنَّهُمَا لَيُعَذَّبَانِ، وَمَا يُعَذَّبَانِ فِي كَبِيرٍ، أَمَّا أَحَدُهُمَا فَكَانَ لاَ يَسْتَتِرُ مِنَ البَوْلِ، وَأَمَّا الآخَرُ فَكَانَ يَمْشِي بِالنَّمِيمَةِ» ثُمَّ أَخَذَ جَرِيدَةً رَطْبَةً، فَشَقَّهَا نِصْفَيْنِ، فَغَرَزَ فِي كُلِّ قَبْرٍ وَاحِدَةً، قَالُوا: يَا رَسُولَ اللَّهِ، لِمَ فَعَلْتَ هَذَا؟ قَالَ: «لَعَلَّهُ يُخَفِّفُ عَنْهُمَا مَا لَمْ يَيْبَسَا».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዓባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
"ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለት ቀብሮች በኩል አለፉና እንዲህ አሉ ' እነርሱ እየተቀጡ ነው። (በናንተ እይታ) ትልቅ በሆነ ወንጀልም አይደለም የሚቀጡት። አንደኛቸው ከሽንት አይጥራራም ነበር። ሌላኛው ደግሞ ነገር በማመላለስ የሚዞር ነበር።' ቀጥለውም እርጥብ ቅጠል በመያዝ ለሁለት ሰነጠቁትና በእያንዳንዱ ቀብር ላይ አንድ አንድ ተከሉ። ሶሐቦችም 'የአላህ መልክተኛ ሆይ! ለምን ይህን ፈፀሙ?' ብለው ጠየቁ። እርሳቸውም ‘ቅጠሎቹ እስካልደረቁ ድረስ ከነርሱ ላይ ቅጣቱን ያቀልላቸዋል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።' ብለው መለሱ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለት ቀብሮች በኩል አለፉና እንዲህ አሉ፦ የነዚህ ሁለት ቀብር ባለቤቶች እየተቀጡ ነው። አላህ ዘንድ ትልቅ ወንጀል ቢሆንም በናንተ እይታ ግን ትልቅ በሆነ ወንጀል አይደለም የሚቀጡት። አንደኛው: በሚፀዳዳ ወቅት ሰውነቱንና ልብሱን ከሽንት መጠበቅን ትኩረት አይሰጠውም ነበር። ሌላኛው ደግሞ በሰዎች መካከል ነገር በማመላለስ ይዞር ነበር። በሰዎች መካከል መጎዳዳትን፣ ልዩነትን ማምጣትና ሀሜትን አስቦ የሌላን ሰው ነገር ያዋስድ ነበር።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነገር ማሳበቅ (ማዋሰድ) እና ከሽንት መጥራራትን መተው ከትላልቅ ወንጀሎች የሚመደብና ከቀብር ቅጣት ምክንያቶችም አንዱ ነው።
  2. ጥራት የተገባው አላህ እንደ ቀብር ቅጣት የመሰሉ አንዳንድ የሩቅ ምስጢሮችን ለርሳቸው መግለጡ የነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የነቢይነት ምልክት ግልፅ ለማድረግ ነው።
  3. ቅጠልን ለሁለት ሰንጥቆ ቀብር ላይ ማድረግ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ላይ ብቻ የተለዩበት ስራ ነው። ምክንያቱም አላህ ለርሳቸው የቀብሩን ባለቤቶች ሁኔታ አሳውቋቸው ነውና ያደረጉት። የቀብርን ባለቤቶች ሁኔታ አንድም የሚያውቅ ስለሌለ ከርሳቸው ውጪ ያለን አካል በርሳቸው አንቀይስም (የርሳቸው ተመሳሳይ ብይን አንሰጠውም)።