عَنْ عَمْرِو بْنُ سُلَيْمٍ الأَنْصَارِيُّ قَالَ: أَشْهَدُ عَلَى أَبِي سَعِيدٍ قَالَ: أَشْهَدُ عَلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«الغُسْلُ يَوْمَ الجُمُعَةِ وَاجِبٌ عَلَى كُلِّ مُحْتَلِمٍ، وَأَنْ يَسْتَنَّ، وَأَنْ يَمَسَّ طِيبًا إِنْ وَجَدَ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከዐምር ቢን ሱለይም አልአንሷሪይ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: "አቡ ሰዒድ እንዲህ እንዳለ እመሰክራለሁ: 'የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ እንዳሉ እመሰክራለሁ:
"ለአቅመ አዳም በደረሰ ሰው ላይ ሁሉ የጁሙዓ ቀን መታጠብ፣ ጥርሱን ሊፍቅና ካገኘም ሽቶ መቀባቱ ግዴታ ነው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከሙስሊሞች መካከል ጁሙዓ ሊሰግድ ግዴታ የሆነበት የደረሰ ወንድ ልጅ ሁሉ የጁሙዓ ቀን መታጠቡ ልክ እንደ ግዴታ አፅንኦት የተሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገለፁ። በመፋቂያና በመሳሰሉት ጥርሱን ማፅዳቱም፤ እንዲሁም ማንኛውም መልካም መዓዛ ያለውን ሽቶ መቀባቱንም አፅንኦት የተሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በሁሉም የደረሰ ሙስሊም ወንድ ላይ የጁሙዓ ቀን መታጠብ እጅግ የሚወደድ መሆኑ አፅንኦት የተሰጠው ጉዳይ እንደሆነ እንረዳለን።
  2. ለአንድ ሙስሊም ንፅህናና መጥፎ ሽታን ማስወገድ በሸሪዓ የሚፈለግ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።
  3. የጁመዓ ቀንን ማላቅና ለርሱ መዘጋጀት እንደሚገባ እንረዳለን።
  4. የጁመዓ ቀን መፋቅ ተወዳጅነት አፅንኦት የተሰጠው ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።
  5. ለጁሙዓ ከመሄድ በፊት ጥሩ መዓዛ ያለው ማንኛውንም ሽቶ መቀባት እንደሚወደድ እንረዳለን።
  6. ሴት ልጅ ለሶላት ወይም ለሌላ ጉዳይ ከቤቷ የወጣች ጊዜ ለርሷ ሽቶ መቀባት ክልክል መሆኑን የሚጠቁም ሐዲሥ ስላለ አይፈቀድላትም።
  7. ሐዲሱ ላይ "ሙሕተሊም" በማለት የተፈለገው አቅመ አዳም የደረሰ ማለት ነው። አቅመ አዳምነት በተለያዩ ምልክቶች ይታወቃል። ሶስቱን ወንዶችም ሴቶችም የሚጋሩት ነው። እነርሱም: አንደኛ: አስራ አምስት አመት መሙላት፤ ሁለተኛ: ሸካራ ፀጉር ብልት ዙሪያ የበቀለ ጊዜ፤ ሶስተኛ: በህልም ወይም ከህልም ውጪ እንኳ ቢሆን በስሜት የዘር ፈሳሽ ማፍሰስ ነው። አራተኛው ምልክት ሴቶች ላይ ብቻ የተገደበ ነው። እርሱም: የወር አበባ ነው። ሴት ልጅ የወር አበባ ከፈሰሳት ጊዜ ለአቅመ ሄዋን ደርሳለች ማለት ነው።