عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ:
إِنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ نَهَى أَنْ يُسْتَنْجَى بِرَوْثٍ أَوْ عَظْمٍ، وَقَالَ: «إِنَّهُمَا لَا تُطَهِّرَانِ».

[صحيح] - [رواه الدارقطني] - [سنن الدارقطني: 152]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
«ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - በፋንዲያ ወይም በአጥንት ኢስቲንጃእ (ከተፀዳዱ በኋላ ከማዳረቅ) ከለከሉ። "ሁለቱም አያፀዱም።" ብለዋል።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ዳረቁጥኒይ ዘግበውታል።] - [ሱነን ዳረቁጥኒይ - 152]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከሸና ወይም ሰገራውን ከተጠቀመ በኋላ በእንስሶች አጥንት ወይም በፍጋቸውና በፋንዲያቸው ከማደራረቅ ከለከሉ። እንዲህም አሉ: እርሷ ነጃሳን አታስወግድምም አታፀዳምም።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አንዳንድ የመፀዳዳትና የኢስቲንጃእ ስነስርዓት መገለፁ።
  2. በፋንዲያ (ፍግ) ኢስቲጅማር ማድረግ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ወይ ነጃሳ ስለሆነ ነው ወይም የጂን እንስሶች ቀለብ ስለሆነ ነው።
  3. በአጥንት ኢስቲጅማር ማድረግ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ወይ ነጂስ ነው። ወይም ለጂኖች ምግብ ስለሆነ ነው።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (33)
ተጨማሪ